Abruzzi Media
11/09/2022
🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼
እንኳን ለ 2015 ዓ.ም አዲስ ዓመት
በሰላም አደረሳችሁ
🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼
አዲሱ አመት የሰላም፤የጤና፤ የደስታ እና ስኬት እንዲሁም የከፍታ ዘመን እንዲሆንልሆ እንመኛለን።
🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼
መልካም አዲስ አመት
🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼
🇪🇹🇪🇹🇪🇹
💚💛❤️
02/06/2022
The 1st Ethiopian National Youth Olympic Games have started.
The inauguration of ethiopian National Youth Olympic Games kicked off today at the Hawassa University international Stadium.
Click the link to see more...
Abruzzi Media – Home News and Entertainment The 1st Ethiopian National Youth Olympic Games have started. The inauguration of ethiopian National Youth Olympic Games kicked off today at the Hawassa University international Stadium. More than 4,000 participants from all regions, Addis Ababa and Dire Dawa City Administration will participate in 1...
20/12/2021
ከዚህ በፊት ስለኢትዮጵያ ጉዳይ ከአስር ጊዜ በላይ ስበስባ የተቀመጠው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የፀጥታው ምክር ቤት ዛሬ ሰኞ በኢትዮጵያ ጉዳይ ለመነጋገር ስብሰባ እንደሚቀመጥ ታውቋል።
ምክር ቤቱ ዛሬ በ “any other business” ስር በኢትዮጵያ ስላለው ሁኔታ የሚወያይ ሲሆን ስብሰባው እንዲካሄድ የጠየቁት ፦
🇪🇪 ኢስቶኒያ
🇫🇷 ፈረንሳይ
🇮🇪 አየርላንድ
🇳🇴 ኖርዌይ
🇬🇧 ዩናይትድ ኪንግደም
🇺🇸 አሜሪካ ናቸው።
የተመድ የሰብአዊ ጉዳዮች የአስቸኳይ ጊዜ ማስተባበሪያ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ማርቲን ግሪፊትስ በኢትዮጵያ ያለውን የሰብአዊ እርዳታ ጉዳይን በተመለከተ ለፀጥታው ም/ ቤት አባላት አጭር ማብራሪያ ይሰጣሉ ተብሏል።
በትግራይ ክልል ውስጥ ጦርነት ከተቀሰቀሰ ጊዜ አንስቶ የተመድ ፀጥታው ምክር ቤት ስለኢትዮጵያ ጉዳይ ከአስር ጊዜ በላይ ስብሰባ የተቀመጠ ሲሆን የዛሬው ስብሰባ ባለፈው ሳምንት የተመድ የሰብአዊ መብቶች ም/ቤት ልዩ ስብሰባ አካሂዶ ከጦርነቱ ጋር በተያያዘ የተከሰቱ የመብት ጥሰቶችን የሚመረምር ዓለም አቀፍ የባለሙያዎች አካል እንዲቋቋም በድምጽ ብልጫ ከወሰነ በኋላ ነው።
https://www.securitycouncilreport.org/whatsinblue/2021/12/ethiopia-meeting-under-any-other-business.php
06/12/2021
ከመላው ዓለም ወደ #ኢትዮጵያ ለሚደረገው " ታላቅ ጉዞ ወደ ሐገር ቤት " የ30% ቅናሽ ማዘጋጀቱን የኢትዮጵያ አየር መንገድ በዛሬው ዕለት አሳውቋል።
አየር መንገዱ ፥ " ከአሁን ጀምሮ እስከ ታህሳስ 11/ 2014 ዓ.ም ተመዝግበው ትኬትዎን ይግዙ ። ከታህሳስ 23/2014 ዓ.ም እስከ ጥር 23 2014 ዓ.ም ይጓዙ " ሲል መልዕክቱን አስተላልፏል።
Abruzzi media'ን በተለየያዩ አማራጮች ይከታተሉ
በ youtube
https://youtube.com/channel/UCSTMi4rzpPsP71kAw9cbEPg
በ Facebook
https://www.facebook.com/Abruzzi-Media-104580105333946/
በ Telegram
https://t.me/Abruzzimedia
19/11/2021
ህብረተሰቡ የመለያ ቁጥሩ 003-100 የሆነውን የጄኖቪያን ፍራፍሬና ለውዝ እንዳይጠቀም ተከለከለ!
ህብረተሰቡ የመለያ ቁጥሩ 003-100 የሆነውን የጄኖቪያን ፍራፍሬ እና ለውዝ የተባለ ስናክ ምግብ ምርት እንዳይጠቀም የኢትዮጵያ የምግብና መድኃኒት ባለስልጣን አሳሰበ፡፡የአለም አቀፍ የምግብ ደህንነት ማስጠንቀቂያ ተቋም ፋብሪካውን ዋቢ አድረጎ ለኢትዮጵያ ምግብና መድኃኒት ባለስልጣን በማለከው መረጃ መሠረት÷ የጄኖቪያን ፍራፍሬ እና ለውዝ የተባለ ስናክ ምግብ ምርት ሊስቴሪአ ሞኖሳይቶጅን በተባለ ጎጂና ገዳይ ተህዋስያን መበከሉ ተረጋግጧል፡፡
በመሆኑም ህብረተሰቡ የመለያ ቁጥሩ 003-100 የሆነውን እንዲሁም የተመረተበት ቀን ቤስት ቢፎር ጃኗሪ 12 2023 የሆነ የምግብ ምርት እንዳይጠቀም ባለስልጣኑ አሳስቧል፡፡ከባለስልጣኑ ፌስቡክ ገጽ ያገኘነው መረጃ እንዳመላከተው÷ ማንኛውም የህረተሰብ ክፍልና የሚመለከተው አካልም ከላይ የተገለፀውን ምርት ሲያገኝ በስልክ ቁጥር 8482 እና በአካባቢ ለሚገኝ ተቆጣጣሪ አካል በመጠቆም እንዲተባበር የኢትዮጵያ ምግብና መድኃኒት ባለስልጣን ጥሪ አቅርቧል፡፡
Abruzzi media'ን በተለየያዩ አማራጮች ይከታተሉ
በ youtube
https://youtube.com/channel/UCSTMi4rzpPsP71kAw9cbEPg
በ Facebook
https://www.facebook.com/Abruzzi-Media-104580105333946/
በ Telegram
https://t.me/Abruzzimedia
Click here to claim your Sponsored Listing.
Category
Contact the business
Telephone
Address
Hawassa
Awassa