Wonde Multi-Media
02/05/2026
ዩናይትድ ኪንግደም በመካከለኛው ምስራቅ የሚሰማራ ‘ስካይሃመር’ የተሰኘ ፀረ-ድሮን ሚሳይል ይፋ አደረገች!
// ዩናይትድ ኪንግደም ዝቅተኛ ወጪ የሚጠይቁ የጥቃት ድሮኖችን ለመምታት የሚያስችላትን ‘ስካይሃመር’ (Skyhammer) የተሰኘ አዲስ የintercepting ሚሳይል በተሳካ ሁኔታ መሞከሯን ገልጻለች።
በብዛትና በአነስተኛ ወጪ ለማምረት በሚያስችል ስልት (Affordable mass) የተገነባው ይህ የመከላከያ ስርዓት፣ እስከ 30 ኪሎ ሜትር የሚደርስ የርቀት ሽፋን ያለው ሲሆን፤ እንደ ‘ሻሄድ’ ያሉ ሰው አልባ አውሮፕላኖችን ውድ የሆኑ ሚሳይሎችን ሳይጠቀሙ ለማክሸፍ ታስቦ የተሰራ ነው።
የእንግሊዝ መከላከያ ሚኒስቴር እንዳረጋገጠው፣ የሚሳይል ስርዓቱን የማሰማራት ስራ በዚህ ወር የሚጀመር ሲሆን፤ በዋናነት በመካከለኛው ምስራቅ የሚገኙ ወታደራዊ ይዞታዎችንና የጋራ ደህንነት ተገዢ የሆኑ ተቋማትን ጥበቃ ለማጠናከር ይውላል።
ይህ እርምጃ በዘመናዊ የአየር መከላከያ ስትራቴጂ ላይ የታየ ግልጽ ለውጥ መሆኑ የተመላከተ ሲሆን፤ ትኩረቱም እጅግ ውስብስብ የሆኑ የጦር መሳሪያዎችን ከመጠቀም ይልቅ፣ ወቅታዊ ስጋቶችን በብዛትና በአነስተኛ ወጪ መመከት በሚያስችል ቴክኖሎጂ ላይ መሆኑን ያሳያል።”
ለተጨማሪ መረጃ ፔጃችንን ይከተሉ !
27/04/2026
ሆርሙዝ ዋነኛ የኢራን መደራደሪያ ሆኗል
// ኢራን የሆርሙዝ ሰርጥን ሙሉ ለሙሉ በመክፈት በምላሹ አሜሪካ ጦርነቱን እንድታቆም እና በኢራን ወደቦች ላይ የጣለችዉን እገዳ እንድታነሳ ለአደራዳሪዎች አዲስ ሀሳብ አቀረበች።
አሜሪካ በዚህ ሀሳብ ከተስማማች የኑክሌያር ፕሮግራም ጥያቄዎቹን ለብቻው መነጋገር እንችላለን ስትል ኢራን አዲስ ምክረ ሀሳብ አቅርባለች።
ኢራን ይህንን የመደራደሪያ ሀሳብ ማቅረቧን ተከትሎ የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ከከፍተኛ የደህንነት አባሎቻቸው ጋር የተወያዩ ሲሆን የኢራንን የመደራደሪያ ሃሳብ ይቀበሉታል ወይም አይቀበሉትም በሚለው ጉዳይ ላይ ትራምፕ ይፋዊ ምላሽ ይሰጣሉ።
(አዩዘሀበሻ)
ለተጨማሪ መረጃ ፔጃችንን ይከተሉ !!
27/04/2026
ቪላድሚር ፑቲን ለኢራን ያላቸውን ድጋፍ በይፋ አስታወቁ !
// በመካከለኛው ምስራቅ ያለው ውጥረት በጨመረበት በዚህ ወቅት፣ የሩስያው ፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን የኢራኑን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አባስ አራግቺን በሴንት ፒተርስበርግ ተቀብለው አነጋግረዋል።
ፑቲን በዚሁ ወቅት፣ ኢራን አሁን ያለችበትን "አስቸጋሪ የጦርነት ወቅት" በድል እንደምትሻገር ያላቸውን እምነት ገልጸዋል።
"ሰላም በአፋጣኝ እንዲሰፍን እና የኢራን ጥቅም እንዲከበር ማንኛውንም ድጋፍ እናደርጋለን" ሲሉም ቃል ገብተዋል።
ኢራን የሆርሙዝ ወሽመጥን በድጋሚ ለመክፈት ለአሜሪካ ጥያቄ ማቅረቧ ተሰምቷል። ሆኖም የኑክሌር ድርድሩ ለሌላ ጊዜ እንዲቆይ እንደምትፈልግ ዶቼቬለ በዘገባው ጠቅሷል።
ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ የኢራንን ጥያቄ ማጤናቸው ቢነገርም፣ ዋይት ሃውስ ግን "ካርዱ ያለው በእኛ እጅ ነው" አሜሪካ በሚል በድርድሩ ላይ ያላትን የበላይነት ገልጸዋል።
አባስ አራግቺ በበኩላቸው፣ ባለፈው ሚያዝያ በፓኪስታን የተደረገው ድርድር ውጤት ሳያመጣ የቀረው በአሜሪካ "ከመጠን ያለፈ ፍላጎትና ግትርነት" ምክንያት ነው ሲሉ ወቅሰዋል።
የሆርሙዝ ወሽመጥ መዘጋት በዓለም አቀፍ የነዳጅ አቅርቦት ላይ ከፍተኛ ቀውስ እየፈጠረ በመሆኑ፣ አሁን የሚደረጉት የዲፕሎማሲ ጥረቶች ለዓለም ኢኮኖሚ ወሳኝ ናቸው።
በ ሔዋን ጌታቸው
ለተጨማሪ መረጃ ፔጃችንን ይከተሉ !
Click here to claim your Sponsored Listing.
Category
Contact the public figure
Telephone
Website
Address
Awassa