Addis Condo Winners

Addis Condo Winners

Share

06/10/2024

Most places in Addis also there were some shock !

04/02/2024

የጨረታ ማስታወቂያ

የአዲስ አበባ ቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን ያለበትን የፋይናንስ እጥረት በመፍታት ተጨማሪ ወጪ ቆጣቢ ቤቶችን ገንብቶ ዜጎችን ተጠቃሚ ለማድረግ እንዲችል ከዲዛይን ግንባታ ቢሮ ጋር በመሆን በመንግስት በተመደበ ካፒታል በጀት በተለያዩ ክፍለ ከተሞች ተገንብተው የተጠናቀቁ 3,146 የመኖሪያ ቤቶችን እና 306 የንግድ ቤቶችን በድምሩ 3,452 ቤቶችን ባሉበት ሁኔታ በጨረታ አወዳድሮ በሽያጭ ማስተላለፍ ይፈልጋል፡፡

ማንኛውም ለጨረታ የቀረቡ የመኖሪያ እና የንግድ ቤቶችን ለመግዛት የሚፈልግ ሁሉ ማንነቱን የሚገልጽ መታወቂያ በመያዝ የጨረታ ሰነድ ከ27/05/2016 ዓ.ም ጀምሮ እስከ 20/06/2016 ዓ.ም ድረስ ቅዳሜን እስከ 11፡00 ሰአት እና እሁድ ግማሽ ቀን ጨምሮ ዘወትር በስራ ቀናት ከጠዋቱ 1፡30 እስከ ማታ 1፡30 ድረስ በመቅረብ የማይመለስ ብር 1000.00(አንድ ሺህ) በመክፈል የጨረታ ሰነዱ መግዛት የሚቻል መሆኑን እየገለጽን የሰነድ መሸጫ ቦታ ከዚህ በታች ባለው ሰንጠረዥ ተመላክቷል

20/04/2023

ለጋራ ህንፃ መ/ቤት/ህ/ሥራ/ማህበር በፍቃደኝነት ለተደራጅታችሁ ጥሪ ቀረበ

በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በቤቶች ልማትና አስተደዳር ቢሮ የ2005 ዓ.ም በ20/80 እና 40/60 የቤት ልማት ፕሮግራም ተመዝግባችሁ አሁን መንግስት ባመቻቸው የጋራ ህንፃ መ/ቤት/ህ/ሥራ/ማህበር በፍቃደኝነት ተደራጅታችሁ ቤት ለመገንባት የተመዝግባችሁና አሰፈላጊውን መረጃ አሟልታችሁ ስም ዝርዝራችሁ በግሩፕ ተደልድሎ ለህብረት ሥራ ማህበራት ኤጀንሲ የተላከ መሆኑ ይታወቃል።

ይሁንና ከየግሩፕ አስተባበሪዎች አድራሻቸውን ማግኘት ያልቻልን ተመዝጋቢዎች በሙሉ ከዚህ ቀደም በተደጋጋሚ ማስታወቂያዎች በአካል ቀርባችሁ መረጃ እንድትሰጡ ብትጠየቁ እና ቀርበው ሪፖርት እንድታደርጉ ብትባሉ ሪፖርት ያላደረጋችሁ አባላትን እና በተለያየ መልኩ ቅድመ ክፍያውን መክፈል አንችልም ያላችሁ የመተካካት ስራ በቢሮው በኩል እንዲሰራ በሚል ውሣኔ መሰረት ተቋሙ የሚከተሉትን ውሳኔዎች አስተላልፏል:-

1. B+G+9 የህንፃ ከፍታ ላይ 42 የነበረው የቡድን ድልድል ቡድን 1፣2እና 3 የታጠፈ መሆኑንና በነዚህ ቡድን የነበራችሁ ተመዝጋቢዎች ድልድሉን በማየት ወደ ተመደባችሁበት ቡድን አስተባባሪዎች ሪፖርት እንድታደርጉ፤

2. የ2B+G+13 የነበረው 15 ቡድን ባላችሁበት ሲሆን ተጠባባቂዎችን ሙሉ ለሙሉ በክፍት ቦታዎች ላይ በመደልደል የተሟላ መሆኑን፤

3. ተጠባባቂ የነበራችሁ ተመዝጋቢዎች 2B+G+13 ላይ ሙሉ ለሙሉ የተመደባችሁ በመሆኑ ስም ዝርዝርራችሁን በማየት ለቡድን አስተባባሪዎች ሪፖርት እንድታደርጉ በB+G+9 በተጠባባቂነት የነበራችሁ ዝርዝራችሁን በቅደም ተከተላችሁ መሠረት ፖስት የምናደረግ በመሆኑ ያልተመደባችሁ በትዕግስት በተጠባባቂነት እንድትቆዩ እናስታውቃለን፤

በመጨረሻም ከቢሮው እና ከህብረት ሥራ ማህበራት ኤጀንሲ ውጪ የሚለጠፉ ማስታወቂያዎችን መከተል እንደሌለባችሁ እና ቢሮው በህጋዊ መንገድ ኃላፊነት ወስዶ ከሚለቃቸው መረጃዎች ውጪ በተዛባ መረጃ እንዳትሳሳቱ እናሳስባለን ፡፡

የአዲስ አበባ ቤቶች ልማት እና አስተዳደር ቢሮ

ሙሉ ስማችሁን ከታች ባለው የቴሌግራም ሊንክ ተጭናችሁ ማግኘት ትችላላችሁ

https://t.me/housinginaddisababa/9857

08/04/2023

የ14ኛ ዙር የ20/80 እና የ3ኛ ዙር የ40/60 የጋራ መኖሪያ ቤት እድለኞች ውል የማዋዋል ሂደት ለ30 የስራ ቀናት ተራዘመ

የአዲስ አበባ ቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን በ14ኛ ዙር የ20/80 እና 3ኛ ዙር የ40 /60 የጋራ መኖሪያ ቤቶችን እጣ አውጥቶ ለባለ እድለኞች ለማስተላለፍ ከጥር 1 ቀን 2015 ዓ.ም. ጀምሮ እስከ መጋቢት 26/2015 ዓ.ም ውል ሲያዋውል መቆየቱ ይታወቃል :: የመወያያ ጊዜውም መጋቢት 26/2015 ዓ.ም. ተጠናቋል፡፡ ይሁን እንጂ ባለፉት 60 የስራ ቀናት አስፈላጊውን ቅድመ ሁኔታዎችን በማጠናቀቅ መዋዋል ካለባቸው 25,773 መካከል ውል የተዋዋሉት 1,835 ብቻ በመሆናቸው ቀሪዎቹ በፍርድ ቤት፣ በግዳጅ ፣ በወሊድና በሌሎችም ምክንያቶች ቀርበው መዋዋል ላልቻሉ ውል እንዲዋዋሉ ለማድረግ እና ፕሮሰስ ጀምረው ያላጠናቀቁትን እንዲያጠናቅቁ ለማስቻል ኮርፖሬሽኑ በአዋጅ ቁጥር 64//2011 አንቀፅ 22 ንኡስ አንቀጽ 2 መሰረት እስካሁን ውል ያልተዋዋሉ የቤት እድለኞችን ማዋዋል እንዲያስችል ከመጋቢት 27/2015 ዓ.ም ጀምሮ 30 የስራ ቀናት ያራዘመ መሆኑን እያሳወቅን በነዚህ ቀሪ ቀናት ውስጥ ቀርቦ ያልተዋዋለ ማንኛውም የቤት እድለኛ ቤቱን እንዳልፈለገው ተቆጥሩ ለኮርፖሬሽኑ ተመላሽ የሚደረግ መሆኑን እንዲያውቁት ለማሳሰብ እንወዳለን ፡፡

በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር
የቤቶች ልማት እና አስተዳደር ቢሮ

________________
በገጻችን የምናቀርባቸውን መረጃዎች በአማራጭነት በቴሌግራም ቻናላችን ለማግኘት ከታች ያለውን ሊንክ ይጫኑ።
👇👇👇👇👇
t.me/housinginaddisababa
እንዲሁም፦

Want your business to be the top-listed Media Company in Addis Abeba?
Click here to claim your Sponsored Listing.

Telephone

Address


Addis Abeba