CMTV
16/05/2026
በክርስቶስ ተልዕኮ ቤተክርስቲያን የመንፈስ ቅዱስ ምሽት አገልግሎት
ርዕስ ፦ ዛሬ ክብሩን ታያላችሁ
- ፈተናዎቻችን እድሎች ናቸው
- ፈተናዎች የትልልቅ ታምራት መወለጃዎች ናቸው ።
- ፈተናዎች ኮሳሳ እንዳንሆን አቅመ ቢስ እንዳንሆን መንፈሳዊ ጡንቻ መገንቢያዎቻችን ናቸው ።
- ፈተናዎች የክብሩ መገለጫዎች እና ወደ ሚቀጥለው ደረጃ መሸጋገሪያዎቻችን ናቸው ማዕረግ መቀበያዎቻችን ናቸው ።
- በህይወታችን ዉስጥ አለ የምንለው ፈተና መጥፊያችን ሳይሆን መድመቂያችን መክበሪያችን ነው ።
- ፈተናዎች እግዚአብሔርን ማወቂያችን ናቸው ።
- ትልልቅ ታምራት የሚወለደው በፈተናዎች ዉስጥ ነው ።
- እምነት ለፈተናዎች መልስ ሲሰጥ ታምራት ይሆናል ።
- ክብር ማለት የሀይሉ ባለቤት እግዚአብሔር ለኛ ሲታወቅ ወይም ለኛ ሲገለጥ ማለት ነው ።
- ክብር ማለት የሀይሉ ባለቤት እግዚአብሔር ታምራታዊ አድራጊ ሀይሉ በሁኔታዎቻችን ላይ ሲገለጥ ማለት ነው።
- የእግዚአብሔር ክብር ኢየሱስ ክርስቶስ ነው ።
- ኢየሱስ ክርስቶስን ማወቅ ኢየሱስ ክርስቶስን መገንዘብ የእግዚአብሔርን ክብር ማወቅ ነው
- ያለ ክርስቶስ እግዚአብሔርን ማወቅ አይቻልም ።
- እግዚአብሔር ለፍጥረት ለመታወቅ ብሎ እራሱን የገለጠው ራሱን ያስተዋወቀዉ በልጁ በመድሀኒዓለም በኢየሱስ ክርስቶስ በኩል ነው ።
- ኢየሱስ ክርስቶስን ስንቀበል እግዚአብሔርን የምናዉቅበትን ብርሃን እናገኛለን ።
- ኢየሱስን ስንቀበል ስለ እግዚአብሔር ትክክለኛ እዉቀት ይኖረናል እግዚአብሔር ለኛ ያለው ሀሳብ እና እቅድ ይገልጥልናል።
11/05/2026
በክርስቶስ ተልዕኮ ቤተክርስቲያን የግንቦት ወር ትንቢታዊ አዋጅ የእሁድ ሁለተኛው አገልግሎት
ርዕስ:- የዝግጅት ወር
- በተለያዩ የህይወት ጎዳናዎች መዘጋጀት ይኖርብናል።
- የመጀመሪያው ዝግጅት የማንነት ዝግጅት ነው ፤ ማንነታችንን ለእግዚአብሔር ማንነት ማዘጋጀት።
- ትልቅ ክንውን ፣ በረከት ፣ ትልቅ የእግዚአብሔር እጅ የፀሎት መልስ የምንፈልግ ከሆነ በመጀመሪያ ደረጃ ህይወታችን እና ኑሮአችንን ለእግዚአብሔር ማዘጋጀት ይኖርብናል።
- መልሱ የሚመጣው ከራሱ ከሰጪው ጋር ስለሆነ ለሰጪው ዝግጁ የሆነ ቤት እና ህይወት ለስጦታው ዝግጁ ይሆናል።
- ለስጦታው እጃችንን ከመዘርጋታችን በፊት ለሰጪው ልባችንን መክፈት ይኖርብናል።
- የምናዘጋጀው ህይወታችንን ነው ህይወትን የማዘጋጀት እና የማስተካከል ጊዜ ያስፈልገናል።
- ጌታ ሊያመጣ ላለው በጎ ነገር ፤ ሊያደርገው ላለው ታላቅ ነገር የተዘጋጀ የምህረት ዕቃ ለጌታ የሚጠቅም ይሆናል። 2ጢሞ 2: 21
- ዝግጅቱ የክብር የምህረት እቃ ለጌታ የሚጠቅም እቃ እንዳንሆን ከሚያደርጉ ነገሮች ራስን መከልከል ነው።
- የእግዚአብሔርን ማዳን እና ሀይል የምንጠባበቅ መልካም ነገር በመጣ ጊዜ አያልፈንም ፤ ክፉ ነገር ወደ ቤታችን አይገባም።
- እግዚአብሔር ተዘጋጁ የሚለን ልባዊ ፣ የማንነት ዝግጅት ነው።
- የመጀመሪያው ዝግጅት ህይወትን ከእግዚአብሔር መንገድ ጋር የማስተካከል ዝግጅት ነው።
- ነገ ላይ ከእግዚአብሔር ጋር ለመቆየት ከፈለግን ዛሬ ሁኔታዎች ሲቀየሩ ካልተቀየረው ከእግዚአብሔር ጋር መቆም ያስፈልጋል።
- በዙሪያችን እና በጊዜያችን ካለ ነገር ራሳችንን በማንፃት ነው የምንዘጋጀው።
- የልባችንን አቋም በማስተካከል ነው የምንዘጋጀው።
- ሰውን በሰውነት ልኩ እግዘብሔርን በእግዚአብሔርነት ልኩ ማወቅ ትህትና ነው።
- ክርስቶስ ሁለንተናችን እንዲሆን መድሀኒታችን ሀይላችን እንዲሆን ተልኳል።
- የእርሱ ገንዘብ ለመሆን ራሳችንን ማዘጋጀት አለብን።
Click here to claim your Sponsored Listing.
Category
Contact the place of worship
Website
Address
Ararat Round About To Gurd Sholla 1 Street
Addis Ababa
Opening Hours
| Monday | 08:00 - 18:00 |
| Tuesday | 08:00 - 18:00 |
| Wednesday | 08:00 - 18:00 |
| Thursday | 08:00 - 18:00 |
| Friday | 08:00 - 19:00 |
| Saturday | 08:00 - 18:00 |
| Sunday | 07:00 - 15:00 |