Documents Authentication and Registration service
25/05/2026
ስነ ምግባርን ያካተተ የአመራርነት ብቃት ስልጠና ተሰጠ ፡፡
ግንቦት 17 ቀን 2018 ዓ. ም
በሰነዶች ማረጋገጫና ምዝገባ አገልግሎት ለድሬደዋ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት አመራርና ሰራተኞች የህይወት ክህሎትና የአመራር ብቃት አካቶ ትግበራ ስልጠና ተሰጠ።
በተቋሙ የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ አካቶ ትግባራ ስራ ክፍል አዘጋጅነት በድሬደዋ ከተማ ለ አራት ቀናት በተካሄደው የህይወት ክህሎት እና የአመራርነት ብቃት አካቶ ትግበራ እንዲሁም የስራ ላይ ስነ ምግባር ስልጠና ላይ የቅርንጫፍ ጽ/ቤቱ አመራሮችና ባለሙያዎች ተሳትፈዋል።
ከሴቶችና ህጻናት ሚኒስቴር በመጡት አሰልጣኝ የተሰጠው ይህ ስልጠና ሰራተኞች ያላቸውን አቅምና እዉቀት እንዲገመግሙና ክህሎታቸውን ከማጎልበቱ ባሻገር ልምድ እንዲለዋወጡ ከፍተኛ ጠቀሜታ እንደሚኖረው የሰነዶች ማረጋገጫና ምዝገባ አገልግሎት የድሬዳዋ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ስራ አስኪያጅ ወ/ሮ ትእግስት አየለ ገልጸዋል፡፡ ስራ አስኪያጇ አክለውም «እንደዚህ አይነት ስልጠናዎች በየወቅቱ መሰጠት አለባቸው» ሲሉም ያሳሰቡ ሲሆን፤ በሰልጣኞች የነቃ ተሳትፎ እንዲደረግም ጥሪ አቅርበዋል።
የስልጠናዉ አላማ የሕይወት ክህሎቶች ላይ ግንዛቤ ለመፍጠር፣ መሰረታዊ የሆኑ የሕይወት ክህሎቶችን ለይቶ ለመረዳት እና በስራ ቦታ ላይ ምቹ ስነምህዳርን ለመፍጠር አስቻይ ሁኔታን ለመፍጠር እንዲሁም ዜጎች በተሰማሩበት የስራ መስክ ውጤታማ እና ብቁ እዲሆኑ ለማስቻል ያለመ መሆኑ በመድረኩ ላይ ተገልጿል።
ስልጠናው የሴት አመራሮች የአመራርነት ክህሎትን ከማሳደግ ባሻገር የመሪነትን ጽንሰ ሃሳብን ላይ በበቂ ሁኔታ ግንዛቤ ለመስጠት እና ያላቸውንም መልካም ተሞክሮዎች እንዲያዳብሩ ከፍተኛ ጠቀሜታን እንደሚያስገኝ እንዲሁም በሰራ ቦታ ከተገልጋዮች ጋር የሚኖር ተግባቦት እና በተሰማሩበት የስራ መስክ ላይ የሚኖር ስኬታማነትን የሚመለከት የእውቀትና ክህሎት ያካተተ ነበር፡፡
በስልጠናው 49 ሰልጣኛች የተሳተፉ ሲሆን፤ 32 ሴቶች እና 17ቱ ወንድ ሰራተኞች ናቸው፡፡
Click here to claim your Sponsored Listing.
Category
Contact the organization
Telephone
Website
Address
Addis Ababa
29935