DireTube
11/06/2026
1ኛው የኢትዮጵያ 10 ኪ.ሜ የጎዳና ላይ ሩጫ ውድድር የፊታችን እሁድ በባህርዳር ይካሄዳል
1ኛው የኢትዮጵያ 10 ኪ.ሜ የጎዳና ላይ ሩጫ ውድድር የፊታችን እሁድ ሰኔ 07 ቀን 2018 ዓ.ም በባህርዳር ከተማ በታላቅ ድምቀት ይካሄዳል።
የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌደሬሽን በውድድሩ ቅዶመ ዝግጅት ዙሪያ ለመገናኛ በዙሃን መግለጫ ሰጥተዋል።
የፌዴሬሽኑ ከፍተኛ ቴክኒክ ባለሙያዎች ወደ ባህርዳር በማቅናት አስፈላጊውን ስራ እያከናወኑ ሲሆን ተተኪ አትሌቶችና የውድድር እድል ለመፍጠር ዓላማ ያደረገ መሆኑን በመግለጫው ተገልጿል ።
በውድድሩ ላይ የግል ተወዳዳሪዎችን ጨምሮ ከ6 ክለቦች የተውጣጡ 91 አትሌቶች ይሳተፋሉ ።
በውድድሩ ከ1ኛ እስከ 8ኛ ለሚወጡ አትሌቶች የገንዘብ ሽልማት የሚበረከት ይሆናል።
የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን የውድድርና ተሳትፎ ዳይሬክተር ተወካይ አቶ ጊዜ አድነው እና አቶ መሐሪ ነጋሽ መግለጫውን በጋራ ሰጥቷል።
ውድድሩ በአማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን /አሚኮ/ በቀጥታ ይተላለፋል።
(ኢአፌ)
11/06/2026
በሳዑዲ ዓረቢያ ታሰረው የነበሩ አንድ ሺህ 655 ኢትዮጵያውያን በምህረት እንዲፈቱ ተደረገ
የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ሪያድ የሚገኘውን የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ሚሲዮን እና ጂዳ የሚገኘውን ቆንስላ ጽ/ቤት በማስተባበር ባደረገው የዲፕሎማሲ ጥረት በሳዑዲ አረቢያ ለእስር ተዳርገው የነበሩ 1655 ዜጎቻችን የፍርድ ሂደታቸው ተቋርጦ የምህረት አዋጅ እንዲሰጣቸው ተደርጓል።
ይህ ውጤት መንግሥት በውጭ ግንኙነቱ ለዜጋ ተኮር ዲፕሎማሲ በሰጠው ትኩረት የተገኘ ነው።
ከዜጋ ተኮር ዲፕሎማሲ አኳያ በሳዑዲ አረቢያ ቀሪ የዲፕሎማሲ ጥረት የሚሹ ጉዳዮችን በተመለከተም ክትትል እያደረገ ነው።
በዚሁ አጋጣሚ መንግሥት ሕብረተሰቡ ከሕገ ወጥ የሰዎች አዘዋዋሪዎች በማኅበራዊ ሚዲያ የታጀበ ሀሰተኛ ማታለያ ድርጊት የውጭ አገር ጉዞ ራሱን እንዲጠብቅ እያሳሰበ፤ ሕገ ወጥ የሰዎች አዘዋዋሪዎችን የሕግ ተጠያቂ ለማድረግ የተጀመሩ ጥረቶች ተጠናክረው ይቀጥላሉ።
የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር
11/06/2026
ደሞዝ እና አዲሱ በጀት? ዶ/ር ደሳለኝ ጫኔ
ደሞዝ እና አዲሱ በጀት? ዶ/ር ደሳለኝ ጫኔ በዛሬው ዕለት ሰኔ 4/2018 ዓ/ም በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የ 2019 ዓ/ም በአዲሱ በጀት ዙሪያ የ...
Click here to claim your Sponsored Listing.
Category
Contact the business
Website
Address
Addis Ababa