NISS

NISS

Share

07/10/2024

#መልዕክት

ከደቂቃዎች በፊት በአዋሽ ፈንታሌ ተራራ አካባቢ የመሬት መንቀጥቀጥ ተከስቷል።

ይህ የመሬት መንቀጥቀጥ በሬክተር ስኬል 4.9 ተመዝግቧል።
ይህ ክስተት ከአዲስ አበባ በሰሜን ምስራቅ አቅጣጫ በ165 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ባለ አካባቢ የተከሰተ ነው።

ሆኖም የዚህ መሬት መንቀጥቀጥ ንዝረት በደሴ መስመር እስከ ኮምቦልቻ፣ አዲስ አበባ፣ መተሃራ እና ሌሎችም ቦታዎች ድረስ ተሰምቷል። ባለፉት ቀናት አነስተኛ መጠን ያላቸው ተመሳሳይ አይነት የመሬት ንዝረቶች ሲያጋጥሙ መቆየታቸውንም ባለሙያዎች አመልክተዋል።

በዛሬው ሁኔታ አዲስ አበባ ላይ ከዚህ የከፋ ሁኔታ ሊያጋጥም እንደማይችልም ባለሙያዎቹ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።

ዜጎች የመሬት መንቀጥቀጥ በሚያጋጥምበት ወቅት ባለመደናገጥ ራሳቸውን ከአደጋ ሊጠብቁ ስለሚችሉባቸው መንገዶች መረጃ ሊይዙ እንደሚገባም መልእክታቸውን አስተላልፈዋል።

የጥንቃቄ መልእክቶቹን እና የዘርፉን ባለሙያዎች ምክረ ሃሳቦች ከመገናኛ ብዙሃን እንድትከታተሉ መልእክታችንን እናስተላልፋለን።

07/10/2024

በአዲስ አበባ የተለያዩ አከባቢዎች የመሬት መንቀጥቀጥ እንደተከሰተ ታውቋል:: አራብሳ፣ ሰሚት፣ ኢምፔርያል፣ ፊጋ፣ አያት 49፣ ሰሚት፣ ኮዬ ፈጬ ለተወሰነ ጊዜ የመሬት መንቀጥቀጥ መስተዋሉን ገልጸዋል።

07/10/2024

የጎማው ሌባ ታውቋል

ፊልድ ማርሻሉ straight forward ናቸው። ወታደር እንደፖለቲከኛ ማሳጅ እያረገና ፀጉርህን እያሻሸህ አይነግርህም። የወታደር ኢንተርቪው የምወደው ለዚህ ነው። ከዚህ ቀደም ጀነራል አበባውን አይተናል። የሚፈልጉትን ቀጥታ ይነግሩሃል። ስንት ሞት አይቶ ያለፈ ወታደር ካሜራ ፊት ነኝ ብሎ ለ political correctness ሲጨነቅ አታየውም።

በወታደር ሃቀኝነት ፊት የፅንፈኞች ሃሰት የቁንጫ ታህል ያንሳል። ከወታደር ክብር ፊት በኩራት መቆም የሚችል አንድም ሐገር ጠል የለም። ወታደር የሚያወራውን ይኖራል የሚኖረውን ያወራል። „እገሌ ምን ይለኝ ይሆን“ ብሎ ሲጨነቅ አታየውም። የተገነባበት ስነልቦናና የመጣበት መንገድ ያንን እንዲያደርግ አይፈቅደለትም። ወታደር የእውነት ልኩ ሐገሩ ነች። የሚያሳስበው የሐገሩ ክብር ነው። የሚጨነቀው ሰለሐገሩ ህልውና ነው። የወታደር መፈክሩ „እውነቱን ተናግሮ የመሸበት ማደር“ የሚል ነው። አለቀ! የወታደር ንግግር እንደኮሶ ይመርሃል። ግን ከልብ ካደመጥከው መድሃኒት ነው ያሽርሃል።

ሁለቱ ኦቨርዌይት dumb and dumber ከጀነራሉ ንግግር ተከትለው ራስን ነፃ የማውጣት ጥረት አድርገዋል። አንደኛው „እኔ ጀነራሉን አግኝቼ አላውቅም“ ሲል ሌላኛው ደግሞ ማግኘቱን አምኖ „እኔ መሬት ስጡኝ አላልኩም“ ብሎ አስቆናል።

አንዱ ጎረምሳ ያባቱን የመኪና ጎማ ሰርቆ ሽጦ ሲቅም ዋለና እንደመረቀነ ወደቤቱ ተመለሰ አሉ። አባቱ በረንዳ ላይ ተቀምጠው የልጃቸውን መምጣት ሲመለከቱ „ደና ዋልክ ልጄ“ አሉት። የዚህ ግዜ በምርቃና የጦዘው ጎረምሳ አይኑን አፍጥጦ ምን ቢል ጥሩ ነው?
„የምን ጎማ?“ 😂

ስምህ ሳይጠራ ድንገት መጥተህ „የምን ጎማ?“ ካልከን የጎማው ሌባ አንተ እንደሆንክ ራስህን እያስፎገርክ ነው ማይ ብራዘር 😂
የፋራ ነገር ከባድ ነው።

በመጨረሻም ለኢትዮጵያውያን እኔ ናትናኤል የመኮንን ልጅ አንድ ጥያቄ አለኝ .... ሐገር እንዴት በቁራሽ መሬት ትሸቀጣለች ?

07/10/2024

በሳይበር ደህንነት ዙሪያ ያሉ የተሳሳቱ እሳቤዎችና እዉነታዉ


የሳይበር ደህንነትን ማስጠበቅ የ IT department እና ሌሎች የሚመለከታቸዉ አካላት ብቻ ነዉ፤

#እዉነታዉ፡
የሳይበር ደህንትን ማስጠበቅ የጥቂት የሚመለከታቸዉ አካላት ብቻ ሳይሆን ሁሉም ሰዉ ሊተባበርለት የሚገባ ወሳኝ ጉዳይ ነዉ፤ እያንዳንዱ የምህዳሩ ተጠቃሚ ሁሉ ለጥቃት ተጋላጭ ብሎም ጥቃቱን ለመከላከል ደግሞ ሀላፊነት እንዳለበት መረዳት ተገቢ ነዉ፡፡
በመሆኑም ተቋማት የሳይበር ደህንነታቸውን ከማስጠበቅ አኳያ ትኩረት ሰጥተው መስራት ይጠበቅባቸዋል፤ ለዚህም ተገቢውን የሳይበር ደህንነት አደረጃጀት እና የአሰራር ስርአቶችን መዘርጋት፤ ደህንነቱ የተጠበቀ ቴክኖሎጂ መታጠቅ፤ እንዲሁም የሰራተኞቻቸውን የሳይበር ደህንነት ንቃተ ሕሊና በቀጣይነት መገንባት ይጠበቅባቸዋል፡፡

04/10/2024

የሞባይል ባንኪንግ እና የኢንተርኔት ባንኪንግ ማጭበርበር

የሳይበር ፋይናንስ ማጭበርበር ከሚፈጸምባቸው መንገዶች መካከል የሞባይል ባንኪንግ እና የኢንተርኔት ባንኪንግ ማጭበርበር አንዱ ነዉ፡፡

ይህ የሳይበር ፋይናንስ ማጭበርበር ድርጊት የሚፈጸመው አጭበርባሪዎች ኢንተርኔትን በመጠቀም ያልተፈቀላቸውን የኢንተርኔት እና የሞባይል ባንኪንግ ሲስተም አካውንቶችን እንደ ማልዌር፣ ማስገር ወይም ሌላ የማጥቂያ ዘዴዎችን በመጠቀም ጥሰው በመግባት ህጋዊ ያልሆነ የገንዘብ ዝውውር በማድረግ ከፍተኛ የገንዘብ ኪሳራ ሊያስከትል የሚችል ጥሰት የሚፈጽሙበት የማጭበርበር አይነት ነው።

ይህ ዓይነቱ ማጭበርበር በተለምዶ የኦንላይን ባንኪንግ ሥርዓቶች ላይ ባለ ደካማ የደህንነት እና የተጋላጭነት ክፍተቶችን እንዲሁም የተጠቃሚዎችን ባህሪ እና ደካማ ጎን ለመለየት የተዘጋጁ የተለያዩ ዘዴዎችን በመጠቀም ይከናወናል።

የተለመዱ የሞባይል ባንኪንግ እና የኢንተርኔት ባንኪንግ ማጭበርበር አይነቶች

• ማስገር (Phishing)፡- አጭበርባሪዎች ሕጋዊ የባንክ ሰራተኛ በመምሰል ሀሰተኛ ኢ-ሜይሎችን፣ የድምጽ እና የጽሁፍ መልዕክቶችን በመላክ ግለሰቦችን አታለው የይለፍ ቃላቸውን እና መረጃዎቻቸውን እንዲገልጹ በማድረግ የሚፈጸም የማጭበርበር አይነት ነው፤

• እኩይ ሶፍትዌር (Malware)፡ አጭበርባሪዎች የተጠቂውን ኮምፒውተር ወይም ስማርት ስልክ ለማጥቃት የተለያዩ ማልዌሮችን እና ቫይረሶችን ይጠቀማሉ። ማልዌሩ አንድ ጊዜ ከተጫነ በኋላ የተጠቃሚውን የመግቢያ መረጃዎች (login credentials) በመስረቅ ወይም ተጠቃሚዎችን ወደ ማጭበርበሪያ የባንክ ድረ-ገጽ በማዞር ጥቃት ይፈጽማሉ።

• ጣልቃ ገብነት ጥቃት (Man-in-the-Middle Attacks) ፡ ጠላፊዎች በተጠቃሚው እና በባንኩ ድረ-ገጽ ወይም መተግበሪያ መካከል ያለውን ግንኙነት ያቋርጣሉ፣ በዚህም ጥብቅ የሆነ የባንክ መረጃን ለመቆጣጠር፣ ለመቀየር ወይም ለመስረቅ ያስችላቸዋል።
• ማህበራዊ ምህንድስና (Social Engineering) ፡ አጭበርባሪዎች የባንክ ህጋዊ ወኪሎችን በመምሰል የተጠቃሚዎችን ሚስጥራዊ መረጃ (ለምሳሌ የይለፍ ቃል፣ የደህንነት ማለፊያዎችን) እንዲሰጡ ያደርጋሉ።
• ሐሰተኛ የሞባይል ባንኪንግ መተግበሪያ (Fake Banking Apps) ፡ አጭበርባሪዎች ሀሰተኛ የሞባይል ባንኪንግ መተግበሪያዎችን በመስራት እና ወደ ተጠቃሚ በማሰራጨት ተጠቃሚዎች የይለፍ ቃላቸውን እና ጥብቅ መረጃዎችን አሳለፈው እንዲሰጡ ያደርጋሉ።

ወቅታዊና ተጨማሪ የሳይበር ደህንነት መረጃዎችን ለማግኘት፡-
• ድረ ገጽ፦ https://www.insa.gov.et
• ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/INSA.ETHIOPIA
• ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com//featured
• ቴሌግራም፦ https://t.me/insagovet
• ትዊተር፦ https://twitter.com/INSAEthio
• ቲክቶክ፦ https://www.tiktok.com/.gov
• ኢ-ሜይል፡ [email protected]
• የሳይበር ጥቃት ጥቆማ ለመስጠት ነጻ የስልክ መስመር፡933

04/10/2024

ለኢትዮ ሳይበር ቻሌንጅ ፕሮግራም ተሳታፊዎች

የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር ባወጣዉ የሳይበር ቻሌንጅ ፕሮግራም የተመዘገባችሁ እና ወደ ቀጣዩ ዙር ያለፋችሁ ባለ ልዩ ተሰጥዎ ታዳጊዎች በተመዘገባችሁበት የኢ-ሜይል አድራሻ የተላከላችሁን ሊንክ በመጠቀም በ5 ቀናት ውስጥ እንድትሞሉ የተጠየቃችሁትን ሞልታችሁ እንድትልኩ ስንል በአክብሮት እንጠይቃለን።

ለበለጠ መረጃ
0904311833
0904311837
ይደዉሉ።

04/10/2024

Call for Paper

Information Network Security Administration (INSA) will host National Cyber Security Conference on November 9, 2023. The conference invites the submission of research papers on a wide range of topics related to information assurance, intelligence, and information warfare.

For further information: Terefe Feyissa +251-9-13-23-90-36♥️💪💪💪💪👈🕴🙏

04/10/2024

በኬኒያ ናይሮቢ የነበረውን ህዝባዊ አመጽ እንደ ተሞክሮ ።

የኢኮኖሚ ሪፎርሙን ተከትሎ ብዙ ተስፈኞች የተመኙት አልሆነም። ቢያዩት ቢያዩት ምንም የለም። አሁን በተባበረ ክስ የሁሉንም ማህበረሰብ ጉዳይ የሚነካ ኢኮኖሚያዊ አጀንዳን ደጋግሞ በማንሳት ነውጥ የመፍጠር ፖለቲካ ፤ የጃዋር እና ላኪዎቹ ፖለቲካ። የነውጥ ቀማሪዎች ጩኸት የሚሰማ በላቡ እና ወዙ የሚኖር ጤናማ ሃይል የለም። በብልጽግና ጎዳና ያለችው ኢትዮጵያ ውስጥ ህብረተሰባዊ የአስተሳሰብ ለውጥን በስራ እና ስራ ብቻ ነው ማግኘት የሚቻለው። ይህንን እንኳ ያልተረዳ በቁራ ጩኸቱ የሚታወቅ ራሱን “ኤሊት ነኝ” ባዩ በትዕቢት የተወጠረው አካል የአደባባይ ኳኳታውን አጥብቆ እየተመኘ ይገኛል። ይህ መቼም ሊሆን አይችልም።

በየቦታው ያለው የሽፍታ ሃይል በኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ውስጥ እየፈጠረ ያለውን የዜሮድምር ዝቅጠት ውጤት ይህ የዶክተር አብይ መንግስት ተቋቁሞ ወደሚቀጥለው የእድገት ጎዳና በአዲስ ኢኮኖሚ ሪፎርም እየተጓዘ ይገኛል። ሀገርን የማስቀጠል፣ ቀጣዩን ትውልድ በአላማ ደምሮ የማጽናት ተግባርን መንግስት አጠናክሮ እንደሚቀጥል ሲረዳ ጃ-ዋር ዘመቻውን ወደ አደባባይ አመጽ ከፍ አድርጎ የአሜሪካውን አምባሳደር ፣ የጉራጌውን ኢኮኖሚስት፣ የኦሮሞውን+የትግሬውን+የአማራውን ሽፍታ እያጣቀሰ ስሙኝ አግዙኝ እያለ ይገኛል ።

በኬኒያ ናይሮቢ ጎዳናዎች ይህንን አይቷል ፤ ሲጎመጅም ቆይቷል ፤ ብዙ ሀገራትን ጎብኝቶ ጃዋር የቀሰመው “አሁንም ነውጥ’ ‘አሁንም ሽብርን” መቆመር ነው ። ይህ ያሳዝናል። የሰውልጅ እውቀት በሁለት መልኩ ይገለጻል የማይረባ እውቀት አለ፤ የሚረባ እውቀት አለ፤ ጃዋር እውቀቱ ታጥቦ ጭቃ! የማይረባ! ሆኖበት ተቸግሯል።
ምን ይሻለዋል? አበቃሁ።

መልካም የኢሬቻ በዓል ይሁንልን ።😂😂😂

04/10/2024

በሳይበር ደህንነት ዙሪያ ያሉ የተሳሳቱ እሳቤዎችና እዉነታዉ


ያሉኝ መረጃዎች (Data) ያን ያክል አስፈላጊ አይደሉም፤ የሳይበር ጥቃት ቢደርስብኝም ምንም አይደለም ብሎ ማሰብ።

#እዉነታዉ፡
ምንም እንኳን ሰዎች ይህን ቢያስቡም እያንዳንዱ መረጃ ዋጋ ያለዉና የብሄራዊ ደህንነት አደጋ ሊያስከትል ይችላል። በመሆኑም ማንኛዉም መረጃ ጥንቃቄ ሊደረግለት የሚገባ ሀብት ነዉ፡፡
በግለሰቦች ላይ የሚደርስ ጉዳት በግለሰቡ ላይ ብቻ የመቅረት እድሉ ዝቅተኛ ነዉ። ጉዳቱ ወደ ብሄራዊ ደህንነት ስጋት ያድጋል። እነዚህ ጥቃቶች ሲስከሰቱ በግለሰቦችና በተቋማት ላይ የፋይናንስ ኪሳራ፣ የማንነት ስርቆት፣ መልካም ስም ማጉደፍ መሰል ጉዳቶች ይደርሳሉ። በግለሰቦች የሚደርስ ጥቃት ወደ ማህብረተሰቡ ከፍ በማለት ከፍተኛ የስነልቦና ጫናና ኢኮኖሚያዊ ተፅእኖዎች ከመፍጠሩ ባሻገር ብሄራዊ ደህንነት ስጋትም ነዉ።

04/10/2024
04/10/2024

ተቋሙ ስያሜዉን “ከኤጀንሲ” ወደ “አስተዳደር” መለወጡን ገለጸ

ተቋሙ ቀደም ሲል በአዋጅ ቁጥር 808/2006 መሰረት “የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት ኤጀንሲ” ተብሎ ሲጠራ መቆየቱ ይታወቃል። ሆኖም በኢፌዴሪ መንግስት አስፈጻሚ አካላት ስልጣን እና ተግባራት መወሰኛ አዋጅ 1263/2014 አንቀጽ 78(3) በተመለከተዉ መሰረት “የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር” (Information Network Security Administration (INSA) በሚል ስያሜዉ የተለወጠ መሆኑን ለመግለጽ እንወዳለን።

Want your business to be the top-listed Media Company in Addis Ababa?
Click here to claim your Sponsored Listing.

Website

Address


Addis Ababa