Addis Ababa Design And Construction Works Bureau
07/07/2026
ኢንዱስትሪን በሚመለከት፦
የኢትዮጵያ የኢንዱስትሪ ዘርፍ ከፍተኛ ለውጥ እያሳየ ይገኛል። አጠቃላይ የማኑፋክቸሪንግ አቅም ከነበረበት 47 በመቶ ወደ 67 በመቶ ከፍ እንዲል ሰፊ ጥናቶች እና የድጋፍ ስራዎች ተከናውነዋል። ይህ እድገት ከነባሮቹ የኮምቦልቻ፣ የመቐለ እና የሐዋሳ ኢንዱስትሪ ፓርኮች በተጨማሪ አስር አዳዲስ የኢንዱስትሪ ፓርኮችን በመገንባት ከ80 በመቶ በላይ የውጭ ቀጥተኛ ኢንቨስትመንትን መሳብ ተችሏል። በተጨማሪም የውጭ ምርቶችን በሀገር ውስጥ ምርት የመተካት ስትራቴጂ ተግባራዊ ተደርጓል። በዚህም ሲሚንቶ፣ ብረት፣ ብርጭቆ እና ሴራሚክስን የመሳሰሉ ምርቶችን በሀገር ውስጥ በማምረት ብቻ ወደ 5 ቢሊዮን ዶላር የሚጠጋ የውጭ ምንዛሬ መቆጠብ ተችሏል። ዘርፉ እያስመዘገበ ባለው ፈጣን እድገትም በማዕድን ዘርፍ 24 በመቶ፣ በማኑፋክቸሪንግ 20.3 በመቶ እና በኢነርጂ ዘርፍ ደግሞ 23 በመቶ ጭማሪ ታይቷል። ለወደፊቱም ይህን ስኬት ዘላቂ ለማድረግ ትኩረት የተደረገ ሲሆን፣ በሚቀጥለው ዓመት በኢንዱስትሪ ፓርኮች ብቻ የ12.7 በመቶ እድገት እና ከኢንዱስትሪ ምርቶች ኤክስፖርት የ1 ቢሊዮን ዶላር ገቢ ለማግኘት ታቅዷል።
#የጠሚሩምላሾች
07/07/2026
ኤክስፖርትን በሚመለከት
#የጠሚሩምላሾች
07/07/2026
ግብርና እና የምግብ ሉዓላዊነትን በተመለከተ፦
በዘንድሮው የምርት ዘመን 29 ሚሊዮን ሄክታር መሬት በማረስ 1.3 ቢሊዮን ኩንታል ምርት መሰብሰብ መቻሉ እንዲሁም ዘርፉ የ7.7 በመቶ ዕድገት ማስመዝገቡ፤ የኢትዮጵያ ግብርና እያሳየ ላለው መዋቅራዊ ሽግግር ግልጽ ማሳያ ነው። በሀገር አቀፍ ደረጃ የተተገበረው የ‘ሌማት ትሩፋት’ መርሃ-ግብር አስደናቂ ውጤቶችን ያስመዘገበ ሲሆን፣ በተለይም አቮካዶን ወደ ውጭ በመላክ ከአፍሪካ 2ኛ ደረጃን መያዝ መቻሉ ለሀገሪቱ ተጨማሪ ከፍተኛ ገቢ በማስገኘት አስደናቂ ድል እንዲመዘገብ አስችሏል። ከዚህም በላይ ለረጅም ጊዜ በከባድ ድርቅ ይጎዳ የነበረው የቦረና ቀጣና ዛሬ በሰፊ የስንዴ ልማት ተሸፍኖ ማየት መቻሉ የስትራቴጂያዊ ግብርና ስራችንን ስኬታማነት ያረጋግጣል። ምንም እንኳ የዓለም አቀፍ ጫናዎች ቢበዙም፣ የማዳበሪያ እና የነዳጅ ዋጋ ቢንርም፣ በቁርጠኝነትና በጠንካራ ስራ በምግብ ራሳችንን ለመቻልና በአፍሪካ ላይ የተለጠፈውን የረሃብ ታሪክ ለመቀየር በተግባር እየሰራን እንገኛለን፤ ምክንያቱም ምርጫችን ለምኖ መኖር ሳይሆን ሰርቶ ማደር ነው!
#የጠሚሩምላሾች
Click here to claim your Sponsored Listing.
Category
Contact the organization
Address
ስድስት ኪሎ በሚገኘው የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ህንፃ ላይ፡፡
Addis Ababa