Insurance Fund Administration Agency
14/04/2022
23/03/2022
አሉታዊ መጤ ባህሎች በወጣቶች ስብዕና ላይ በሚያስከትለው ተፅዕኖ ለተቋሙ ሰራተኞች ስልጠና ተሰጠ።
------------------- ------- ------ --------
የመንገድ ደህንነትና መድን ፈንድ አገልግሎት በሴቶችና ህፃናት ዳይሬክቶሬት አሉታዊናመጤ ባህሎችና አደንዛዥ ዕፆች በወጣቶች ሰብዕና ላይ በሚያስከትለው ተፅዕኖ ዙሪያ መጋቢት 13 ቀን 2014 ዓ.ም በዲባቤ ሆቴል ስልጠና ተሰጠ።
የዕለቱ ፕሮግራም በማስመልከት የተቋሙ የሴቶችና ህፃናት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ወ/ሮ መሰረት አያሌው የመክፈቻ ንግግር በማድረግ እንኳን ለማርች 8 አደረሳቹህ ብለዋል። ወ/ሮ መሰረት አያሌው በንግግራቸው የወጣቶች ስብዕና ለመገንባት ተቋማችን ከሌሎች ተቋማት ጋር በቅንጅት ለመስራት እንደሚገባ ገልፀዋል።
ከሴቶችና ማህበራዊ ጉዳዮች ሚኒስተር የወጣቶች ስብዕና ባለሙያ አቶ ኑረዲን ሽኩሪ ባቀረቡት ሰነድ ላይ እንደገለፁት አደንዛዥ ዕፆች የሚያስከትሉት ማህበራዊ ቀውስ እንዲሁም የጤና ጉዳት ምርታማነትን በመቀነስ የሀገሪቱን ኢኮኖሚ ጫና ውስጥ ስለሚከት ሁሉም ባለድርሻ አካላት ከሚኒስተር መስሪያቤቱ ጋር በቅንጅት መስራት እንደሚገባ ገልፀዋል።
በመጨረሻም ማርች 8 በማስመልከት እና ተሽከርካሪና ሴቶች በሚሉ ርዕሶች ዙሪያ የመወያያ ሰነድ ቀርቦ ውይይት ተደርጓል።
Click here to claim your Sponsored Listing.
Category
Contact the organization
Telephone
Website
Address
Kazanchis Elily International Hotel Building 2 (3rd & 4th Floor)
Addis Ababa
1288