LDI
04/01/2025
የእንስሳት ልማት ኢንስቲትዩት ድጋፍ ለሚሹ 40 የአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ወረዳ 7 ነዋሪዎች ማዕድ አጋራ
ኢንስቲትዩቱ በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ወረዳ 7 በተቋሙ ዙሪያ ለሚገኙና ድጋፍ ለሚሹ 40 ነዋሪዎች በ50 ሺ ብር ወጪ 4 ኩንታል ዱቄት ዛሬ ድጋፍ አድርጓል።
ድጋፉን ለወረዳው አፈጉባኤ መንግሥቱ መዳልቾ
ያስረከቡት የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር አሥራት ጤራ (ዶ/ር) እንደገሉፁት በክቡር ጠቅላይ ሚኒስትራችን አነሳሽነት የተጀመረውን ማህበራዊ ኃላፊነት ለመወጣት እየሰራ ነው ብለዋል።
ማህበራዊ ድጋፍ ኃላፊነቱን በክረምትና በጋ በጎ አድራጎት አጠናክሮ ከመቀጠል ባሻገር ከወረዳውና በከተማ አስተዳደሩ አርሶአደርና ግብርና ልማት ኮሚሽን ጋር በቅንጅት የሌማት ትሩፋቱን በሙያ እና በግብዓት ድጋፍ እያደረገ መሆኑንም ዋና ዳይሬክተሩ ተናግረዋል።
እንስሳት ልማት ኢንስቲትዩት ካሁን በፊት ለሁለት ቤተሰቦች የመኖሪያ ቤት ከተሟላ የቤት ቁሳቁስ ጋር ከማስረከብ ጀምሮ በየዓመቱ በተለያዩ አውደ በዓላት ድጋፍ ሲያደርግ መቆየቱን ዶ/ር አስራት አስታውሰዋል።
በመጨረሻም ዋና ዳይሬክተሩ ለክርስትና እምነት ተከታዮች የገና በዓል የሰለም፣ የፍቅርና የመተሳሰብ ይሆን ዘንድ መልካም ምኞታቸውን ገልጸዋል።
Click here to claim your Sponsored Listing.
Contact the school
Telephone
Website
Address
Addis Ababa
Opening Hours
| Monday | 09:00 - 17:00 |
| Tuesday | 09:00 - 17:00 |
| Wednesday | 09:00 - 17:00 |
| Thursday | 09:00 - 17:00 |
| Friday | 09:00 - 17:00 |