Divers Media Network - DMN

Divers Media Network - DMN

Share

Photos from Divers Media Network - DMN's post 01/06/2026

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በበሻሻ ድምፅ ሰጡ
*******************

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በትውልድ ቀያቸው በሻሻ ድምፅ ሰጥተዋል።

Photos from Divers Media Network - DMN's post 31/05/2026

‎በ1950ቹ የተለያዩ አገልግሎቶችን ይሰጥ የነበረው የቴፒ መለስተኛ የአየር ማረፊያ ለብዙ አመታት ተቋርጦ የነበረ ቢሆንም ከአቬሽን ባለስልጣንና ለሎች አካላት ጋር በመሆን የሸካ ዞን ዳግም ወደ ስራ ማስገባት ችሏል ።

‎በዚህም የመጀመሪያ በረራ ተጠቃሚዎች እንደገለፁት
‎በትራንስፖርት ዘርፍ በሸካ ዞን ከዚህ በፊት ከፍተኛ ችግር መኖሩን ገልፀው አሁን የተጀመረው በረራ ያለውን እንግልት የቀነሰና ለተገልጋዩ ምቹና ቀልጣፋ የትራንስፖርት አገልግሎት የሰጠ ነው ብለዋል።

‎በተመጣጣኝ ዋጋ የትራንስፖርት አገልግሎት እያገኙ መሆናቸውን የተናገሩት መንገደኞች የመጀመሪያ የአገልግሎቱ ተጠቃሚ በመሆናቸው ከፍተኛ ደስታ እንደተሰማቸው ጠቁመዋል ።

‎የሸካ ዞን እምቅ የተፈጥሮ ሀብት ያለበት በመሆኑ ይህን የቱሪስት መዳረሻ ለማድረግና አካባቢ ላይ ያለውን ምርት ለማስተዋወቅ በረራ አገልግሎት መጀመሩ ትልቅ አስተዋጽኦ እንደሚኖረውም ካፕቴን አብረሃም ጆሴፍ ተናግረዋል።

‎የበረራ አገልግሎት መጀመሩ ለሸካ ዞን ብቻ ሳይሆን በአካባቢ ላይ ትልቅ እድል የፈጠረና ቀልጣፋ የትራንስፖርት አገልግሎት እንዲኖር ያስቻለ መሆኑን የገለፁት ካፒተን አብረሃም ይህም በተመጣጣኝ ዋጋ የቀረበ በመሆኑ መጠቀም አለባችሁ ብለዋል።

‎የፍላይት ቡክንግ አስተባባሪ አቶ ብሩክ በለጠ በበኩላቸው የትራንስፖርት አገልግሎት ለማግኘት booking app የተሰኘውን መተግበሪያ ከአፕስቶር በማውረድ ባሉበት ሆነው ቲኬት መቁረጥ የሚችሉ መሆኑን ተገልጿል ።

‎በዚህም ተገልጋዮች ያለምንም እንግልት መጠቀም መጀመራቸውን የገለፁት አቶ ብሩክ የአካባቢው ማህበረሰብ ይህን አገልግሎት መጠቀም እንዳለበት አሳውቀዋል ።

‎ከዚህ በተጨማሪ ቴፒ ግሪን ኮፊ የፌስቡክ እና ቴሌግራም ገፆች ላይ መረጃዎችን ማግኘት እንደሚቻል ገልፀው ተጠቃሚዎች የሚኖራቸውን አስተያየት በዚህ ላይ ማስቀመጥ እንደሚችሉም ተናግረዋል ።

‎በረራው ሰኞ እና አርብ ከሳምንት ሁለት ጊዜ
‎ዘወትር እንደሚኖር ገልፀው ይህም አካባቢውን ለማስተዋወቅና የቱሪስት መዳረሻ ለማድረግ ትልቅ አቅም አለው ብለዋል።

‎Masha FM

30/05/2026

#ፒኤስጂ አሸናፊ ሆኗል

Want your business to be the top-listed Media Company in Addis Ababa?
Click here to claim your Sponsored Listing.

Telephone

Website

Address


Addis Ababa