Ethio Legal Hub
25/05/2024
የኮንዶሚንየም ቤት ሽያጭ
==============
የኮንዶሚንየም ቤት የደረሰው ሰው ለ3ኛ ወገን በሽያጭ ወይም በስጦታ ሊያስተላልፍ የሚችለው ቤቱን ከገዛ 5 አመት ሲሞላው ብቻ ስለመሆኑ በአዋጅ ቁጥር 19/97 ተደንግጓል። ይሁንና ይህ ጊዜ መቆጠር የሚጀምረው እጣው ከወጣ በኃላ ነው ወይስ እጣውን ተከትሎ ከሚመለከተው የአስተዳደር አካል ጋር ውል ከተደረገበት ጊዜ ጀምሮ ነው የሚለው ሲያከራክር የነበረ ሲሆን በአዋጁ ላይ በግልፅ ባይቀመጥም ከጠቅላላ ድንጋጌዎቹ ይዘት የምንረዳው የኮንዶሚንየም ቤት እጣ ከከተማው አስተዳደር ጋር የቤት ግዢ ውል ለማድረግ መብት የሚሰጥ እንጂ እራሱ የቤት ግዢ ውል አይደለም፡፡ ስለዚህም የኮንዲሚንየሙ ባለቤት ለ3ኛ ወገን በሽያጭ ወይም በስጦታ ማስተላለፍ የሚችለው ቤቱን በገዛ 5 አመት ሲሞላው ነው የሚለው ጊዜ የሚቆጠረው እጣ ከደረሰበት ቀን ጀምሮ ሳይሆን የሚቆጠረው የቤት ሽያጭ ውል ከሚመለከተው የመንግስት አካል ጋር ከተፈፀመበት ቀን ጀምሮ ነው፡፡
/የሰበር መ/ቁ 158899/
=======
Join us on Telegram👇👇
https://t.me/ET_Legalhub
👉 Tiktok 👇
https://vm.tiktok.com/ZMMEL5E2W/
04/05/2024
ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለብርሀነ ትንሳኤው በሰላም አደረሳችሁ።🙏
Ethio Legal Hub መልካም የትንሳኤ በአል እንዲሆንላችሁ ይመኛል።
04/05/2024
ወራሽነት መብት ቢሆንም ሟች ወይም የኑዛዜ አድራጊው በህጉ በተሰጠው መብት መሰረት በሚያደርገው ኑዛዜ ህጋዊ ወራሾቹን የውርስ ሀብት ተካፋይ እንዳይሆኑ ከውርስ ሊነቅላቸው ይችላል።
ከውርስ መንቀል ጋር በተገናኘ ከብዙ በጥቂቱ በአጭሩ እንዲህ አዘጋጅተንላችኋል።
በዚህ ርዕስ ላይ ያዘጋጀነውን ዝርዝር ፅሁፍ ለማንበብ የቴሌግራም ቻናላችንን ይጎብኙ👇
https://t.me/ET_Legalhub
Ethio Legal Hub
10/04/2024
ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለዒድ አልፈጥር በአል በሰላም አደረሳችሁ።
🌙
Click here to claim your Sponsored Listing.
Category
Website
Address
Addis Ababa