Ethio dish and Receiver Technology

Ethio dish and Receiver Technology

Share

21/08/2024

ጀርመናዊው አማካኝ ወደ ቀድሞ ቤቱ የሚመለሰው በነፃ ዝውውር ሲሆን እስከ 2025 ድረሰ የሚያቆየውን የ 1 አመት ኮንትራት ይፈራረማል .... በውሉ ላይም ለተጨማሪ 1 አመት ውሉን የሚያራዝምበት አማራጭ ተካቷል።

Photos from Ethio dish and Receiver Technology's post 04/08/2024

በተከዜ ወንዝ በጀልባ ተሳፍረው ሲጓዙ የነበሩ 12 ሰዎች በድንገተኛ ጎርፍ ህይወታቸው አለፈ

| በዋግ ኽምራ ብሔረ-ሰብ አስተዳደር ከሰሃላ ሰዬምት ወረዳ ወደ ዝቋላ ወረዳ በተከዜ ወንዝ በጀልባ ሲጎዙ የነበሩ 12 ሰዎች በድንገተኛ ጎርፍ ሕይወታቸው አልፏል፡፡

ትናትንት ባጋጠመው አደጋ መነሻቸውን ሰሃላ ሰዬምት ወረዳ መሸሃ ከተማ እና ሰላዝጌ ቀበሌ አድርገው ወደ ዝቋላ ወረዳ ሀገረ- ሰላም ቀበሌ ዘመቁ ደብር ቀብር ለመድረስ ሲጓዙ የነበሩ 26 ሰዎች በጀልባ ተሳፍረው ተከዜ ወንዝን አቋርጠው በመጓዝ ላይ እያሉ ድንገት በተፈጠረ ጎርፍ የ12 ሰዎች ህይወት ማለፉ ተገልጿል፡፡

የዋግ ኽምራ ብሔረሰብ አስተዳደር ተቀዳሚ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ኃይሉ ግርማይ፤ እስካሁን ባለው መረጃ በአደጋው የ12 ሰዎች ህይወት ማለፉን ገልፀው፤ 7 ሰዎች ደግሞ ከፍተኛ ጉዳት ደርሶባቸው ህክምና እየተደረገላቸው እንደሚገኝ ተናግረዋል።

በጀልባው ተሳፍረው ከነበሩት ውስጥ 7 ሰዎች ደግሞ በዋና ራሳቸውን ማዳናቸውንም አቶ ኃይሉ አስረድተዋል።

ተከዜ ወንዝ የበርካታ ወንዝ ገባሮችን የሚቀበል በመሆኑ የውሃ መጠኑ ከፍተኛ ሊሆን ስለሚችል ማህበረሰቡ ግድቡ እስኪጠናቀቅ እንቅስቃሴውን በጥንቃቄ ማድረግ እንዳለበት አቶ ኃይሉ መግለጻቸውን ከዋግ ኽምራ ብሔረ-ሰብ አስተዳደር ከሙዩኒኬሽን መምሪያ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡

የጀልባ ባለቤቶች ከአቅም በላይ በመጫን ሊደርስ ከሚችለው ጉዳት ጥንቃቄ ሊያደርጉ እንደሚገባም አሳስበዋል።

ዋና አስተዳዳሪው በሰሃላ ወረዳ ተከዜ ወንዝ በጎርፍ አደጋ በደረሰው የሰዎች ህይወት ማለፍ የተሰማቸውን ጥልቅ ሃዘን ገልፀው፤ ለሟች ቤተሰቦች እና ለመላው የብሔረሰብ አስተዳደሩ ህዝብ መፅናናትን ተመኝተዋል።

17/05/2024

NOTCOIN መሸጥ የምትፈልጉ አዋሩኝ

Want your business to be the top-listed Media Company in Addis Ababa?
Click here to claim your Sponsored Listing.

Category

Telephone

Address


Addis Ababa