Woyzero kelemework tiruneh secondary school 2013

Woyzero kelemework tiruneh secondary school 2013

Share

14/06/2020

የኮሮና ስርጭት ከክልሎች አንፃር ምን ይመስላል!

ስርጭቱ በዚህ ከቀጠለ እንደ ሐገር በዚህ ሁኔታ ከቀጠለ፣ ማን ይተርፋል? መንግስት ምን ማድረግ አለበት?

ካነበባችሁ በሗላ ሐሳብ ስጡበት ።

አዲስ አበባ፣
በኦሮሚያ አማራ ትግራይ ደቡብ ድሬዳዋና ሀረሪ እንዲሁም አፋር ያሉት ወቅታዊ የኮሮና ቫይረስ ሁኔታ

በኦሮሚያ ክልል ባለፉት 24 ሰዓት የተደረገው የላብራቶሪ ምርመራ 215 ሲሆን ከነዚህ መካከል ነው 15 ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸው የተረጋገጠው።
- 3 ሰዎች ከጉጂ (የ1 ዓመት ህፃን ሴት፣ የ42 ዓመትና የ54 ዓመት ወንድ) ፤ የውጭ ሀገር ጉዞ ታሪክ የሌላቸው፤ በቫይረሱ ከተያዘ ሰው ጋር ንክኪ ያላቸው።
- 2 ሰዎች ከሰበታ (የ47 ዓመት ወንድና የ32 ዓመት ሴት) ፤ የውጭ ሀገር ጉዞ ታሪክ የሌላቸው፤ ወንዱ ከማህበረሰቡ የተገኘ ሴቷ በቫይረሱ ከተያዘ ሰው ጋር ንክኪ ያላት።
- 7 ሰዎች ከቡራዩ (የዕድሜ ክልላቸው ከ21-37 ውስጥ ይገኛል) ፤ የውጭ ሀገር ጉዞ ታሪክ የላቸውም፤ 3 ሰዎች በበሽታው ከተያዘ ሰው ጋር ንክኪ ያላቸው፣ የተቀሩት ከማህበረሰቡ የተገኙ።
- 2 ሰዎች ከለገጣፎ (የ14 ዓመት ወንድና የ21 ዓመት ሴር )፤ የውጭ ሀገር ጉዞ ታሪክ የሌላቸው፤ ከማህበረሰቡ የተገኙ።
- 1 ሰው ከሱሉልታ (የ40 ዓመት ወንድ)፤
የውጭ ሀገር ጉዞ ታሪክ የለውም፤ ከማህበረሰቡ የተገኘ።

በአማራ ክልል ባለፉት 24 ሰዓት የተደረገው ምርመራ 524 ሲሆን ከነዚህ መካከል ነው 23 ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸው የተረጋገጠው።
20 ሰዎች በምዕ/ጎንደር ዞን በሚገኙ ለይቶ ማቆያ ማዕከላት ክትትል ሲደረግላቸው የነበሩ (የውጭ ሀገር የጉዞ ታሪክ ያላቸው) ናቸው።
2 ሰዎች በጎንደር ከተማ በሚገኘው ማራኪ ለይቶ ማከሚያ ማዕከል የነበሩ እንዲሁም 1 ሰው በሰ/ወሎ ዞን በሚገኘው ላልይበላ ለይቶ ማቆያ ማዕከል የነበረ።
በፆታ አኳያ 21 ወንድና 2 ሴት ናቸው ፤ የእድሜ ክልላቸው ከ16 እስከ 22 ዓመት ውስጥ ይገኛል።

ባለፉት 24 ሰዓት ውስጥ የተደረገው 219 የላብራቶሪ ምርመራ ሲሆን ከነዚህ መካከል ነው 9 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው የተረጋገጠው።
ከዘጠኙ መካከል 6 የውጭ ሀገር የጉዞ ታሪክ ያላቸው ሲሆኑ 3 ሰዎች የውጭ ሀገር የጉዞ ታሪክና በበሽታው ከተያዘ ሰው ጋር ግንኙነት የሌላቸው ናቸው።

በደቡብ ክልል ቫይረሱ የተገኘባቸው ሰዎች ቁጥር 44 ደርሷል። ባለፉት 24 ሰዓት የተደረገው የላብራቶሪ ምርመራ 426 ሲሆን ከነዚህ መካከል ነው 2 ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸው የተረጋገጠው።
ታማሚ 1 - የ20 ዓመት ኢትዮጵያዊ የካፋ ዞን ጌሻ ወረዳ ነዋሪ ፤ የውጭ ሀገር ጉዞ የሌለው ፤ በበሽታው ከተያዘ ሰው ጋር ንክኪ ያለው።
ታማሚ 2 - የ36 ዓመት ኢትዮጵያዊ የካፋ ዞን ጌሻ ወረዳ ነዋሪ፤ የውጭ ሀገር ጉዞ ያለው የረዥም ርቀት አሽከርካሪ ፤ በበሽታው ከተያዘ ሰው ጋር ንክኪ ያለው ነው።

በአፋር ክልል በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው የተረጋገጠ ሰዎች ቁጥር 47 ደርሷል። ባለፉት 24 ሰዓት ውስጥ የተካሄደው የላብራቶሪ ምርመራ 147 ሲሆን ከነዚህ መካከል ነው 11 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው የተረጋገጠው።

በድሬዳዋ ከተማ አስተደር 2 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው ተረጋገጧል። በቫይረሱ የተያዙት የ33 እና የ23 ዓመት ወጣቶች ናቸው። ሁለቱም በለይቶ ማቆያ ውስጥ ያሉና አንደኛው ግለሰብ ቀደም ሲል በቫይረሱ ተይዞ በህክምና ማዕከል ውስጥ ካለ ሰው ጋር የቅርብ ንክኪ ያለው ሲሆን ሁለተኛው ደግሞ ከጅቡቲ ተመላሽ ነው።

ባለፉት 24 ሰዓት በሐረሪ ክልል 53 የላብራቶሪ ምርመራ የተደረገ ሲሆን ከነዚህ መካከል ነው 1 ሰው በቫይረሱ መያዙ የተረጋገጠው። በቫይረሱ የተያዘው የ4 ወር ህፃን ወንድ ሲሆን የድሬ ጠያራ ወረዳ ነዋሪ ነው።

Want your public figure to be the top-listed Public Figure in Addis Ababa?
Click here to claim your Sponsored Listing.

Category

Telephone

Website

Address


Addis Ababa