GIFT WATER
የታሸገ ውኃ አምራቾች በዓመት ወጪ ያደርጉ የነበረው 100 ሚሊዮን ዶላርን የሚያስቀር ማስተርባች የተሰኘ ምርት መጠቀም እንዲያቆሙ መወሰኑን የኢትዮጵያ ውኃ፣ ለስላሳ መጠጦች፣ አትክልትና ፍራፍሬ አምራቾች ማኅበር ገለጸ።
የታሸገ ውኃ አምራቾች በተለይም በጥሬ ዕቃ እጥረት ለማምረት ሲቸገሩ መቆየታቸውንና ለዚህም እንደ መፍትሔ ከተወሰዱት ጉዳዮች መካከል ተጨማሪ ግብዓቶችን መጠቀም ማቆም መሆኑን የማኅበሩ ፕሬዚዳንት አቶ አሸናፊ መርዕድ ገልጸዋል።
በውጭ ምንዛሪ እጥረት ምክንያት ከዚህ በፊት ከ20 በላይ የታሸገ ውኃ አምራቾች መዘጋታቸው የሚታወስ ሲሆን አሁንም እነዚህ አምራቾች ወደ ምርት እንዳልተመለሱ አቶ አሸናፊ ገልጸዋል። ሌሎችም ተጨማሪ ድርጅቶች ማምረት ያቆሙ መኖራቸውን አክለዋል።
ማስተር ባች የተሰኘው የውኃ ፕላስቲክ ግብዓት በዋናነት ፕላስቲኩ ውኃ ሰማያዊ ቀለም እንዲኖረው የሚያደርግ መሆኑን የገለጹት አቶ አሸናፊ ይህም በምርቱ ላይ ምንም ተጨማሪ ጥቅም የማያስገኝ በመሆኑ አምራቾቹ መጠቀም እንዲያቆሙ ሰኔ 27 ቀን 2014 ዓ.ም. መወሰኑን ተናግረዋል። ይህም ባለፉት አንድ ዓመት ተኩል ጥናት ሲደረግበት የቆየና ከአካባቢ፣ ከጤና እና ከኢኮኖሚ አንፃር ያለው ጥቅም ግምት ውስት የገባ መሆኑን አብራርተዋል። ‹‹ከዚህ በፊት ምርቱን መጠቀም አስገዳጅ ባይሆንም፣ አምራቾች በራሳቸው ፍላጎት እየተጠቀሙ ነው፤›› ብለዋል፡፡
የፕላስቲክ ውኃ አምራቾች ማስተር ባች የተባለውን ግብዓት ለማስመጣት በዓመት 100 ሚሊዮን ዶላር ወጪ እንደሚያደርጉ ገልጸው ግብዓቱ ጥቅም ላይ እንዳይውል መደረጉ ከፍተኛ ወጪ የሚቆጥብ መሆኑን ገልጸዋል። አምራቾቹ ከመጪው ጥቅምት 2015 ዓ.ም. ጀምሮ ምርቱን ሙሉ በሙሉ መጠቀም እንዲያቆሙ ከኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ውሳኔ መተላለፉንና ጊዜው እስኪደርስ ያላቸውን ምርት ተጠቅመው እንዲጨርሱ ጊዜ እንደተጣቸው አቶ አሸናፊ አብራርተዋል።
በውኃ ፕላስቲክ ምርቶች ውስጥ እንደ ተጨማሪ ግብዓት የሚያገለግለው ማስተር ባች ጥቅም ላይ የዋሉ የውኃ ፕላስቲኮችን መልሶ ለመጠቀም እንደማያስችል ገልጸው ይህም መቅረቱ ፕላስቲኮቹን ወደ ውጭ ለመላክና ለሌሎች ምርቶች ግብዓትነት ለማዋል ይጠቅማል ብለዋል። ለምርቱ የሚወጣው ገንዘብ ሲቀንስ አሁን ካለው የፕላስቲክ ውኃ ዋጋ ላይ ቅናሽ ሊኖር እንደሚችል ይጠበቃል ብለዋል፡፡
ሪፖርተር ጋዜጣ ሀምሌ 6/2014
11/01/2022
ቀን 02/05/2014ዓ/ም
ማስታወቂያ ለስራ ፈላጊዎች፣
ድርጅታችን ጉደራ ዜት ትሬዲንግ የሽያጭ ሰራተኞችን አወዳድሮ መቅጠር ይፈልጋል።
ተፈላጊ ችሎታ፣ በታሸጉ መጠጦች ሽያጭ ሰራተኝነት 2 ዓመትና በላይ የሰራ እና ደረሰኝ መቁረጥ የሚችል
ደመወዝ: በስምምነት
ፍላጎቱ ያለው [email protected] ላይ አስፈላጊ መረጃዎችን ለ0 ተከታታይ ቀናት በመላክ መመዝገብ ይቻላል።
ለበለጠ መረጃ
0966244419 ይደውሉ
08/09/2020
መልካም ጉዞ ጊፍትን ይዞ።
ማስታወቂያ ለሽያጭ ሰራተኞች
የድርጅታችን እህት ኩባንያ ለሆነው ሮሐ የሞተር ዘይትና ቅባት ማከፋፈያ 1 የሽያጭ ባለሙያ ቀጥሮ ማሰራት ይፈልጋል።
ልምድና ፍላጎቱ ያለው በስልክ ቁጥር 0953303030 ደውሎ መረጃ ማግኘት ይችላል።
አድራሻ: አዲስ አበባ ዮሀንስ ቤተ ክርስቲያን አካባቢ
14/11/2018
25/12/2015
ፈጥነው ይመዝገቡ! ይጎብኙ፣ ቤትዎን ይምረጡ!
21/12/2014
ማዕድን ሚኒስቴር 56 የማዕድን ፍለጋ ፈቃዶችን ሰረዘ
ማዕድን ሚኒስቴር ሥራቸውን በአግባቡ አላካሄዱም ባላቸው የአገር ውስጥ የውጭ ኩባንያዎች ተይዘው የነበሩ 56 የማዕድን ፍለጋ ፈቃዶችን ሰረዘ፡፡
ሪፖርተር እንዳስነበበው ኩባንያዎቹ በወርቅ፣ በብረት፣ በከበሩ ድንጋዮችና በሌሎች ማዕድናት ፍለጋ ሥራ ለማካሄድ ከሚኒስቴሩ ፈቃድ ወስደው በገቡት ውል መሠረት ሥራቸውን ሳያካሂዱ ለረጅም ጊዜ የተቀመጡ ናቸው፡፡ ኩባንያዎቹ ፈቃዱ ሲሰጣቸው ባቀረቡት የሥራ ዕቅድ መሠረት የማዕድን ፍለጋ ሥራቸውን ሳያካሂዱ የማዕድን ፍለጋ ቦታዎችን ለዓመታት ይዘው በመቀመጣቸው ዕርምጃው መወሰዱን ምንጮች ተናግረዋል፡፡
‹‹ያለ በቂ ምክንያት የፍለጋ ቦታዎችን ያለሥራ ይዘው ለዓመታት በተቀመጡ ኩባንያዎች ላይ የማዕድን ሥራዎች ፈቃድ አስተዳደሩ ዕርምጃ ወስዷል፤›› ብለዋል ምንጮች፡፡ የሚኒስቴሩ የኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ዕርምጃው መወሰዱን ያረጋገጠ ቢሆንም ዝርዝር መረጃ ከመስጠት ተቆጥቧል፡፡
ማዕድን ሚኒስቴር 272 የማዕድን ፈቃዶች የሰጠ ሲሆን፣ ከእነዚህ ውስጥ 209 የምርመራ ፈቃዶች ሲሆን፣ 63 የማዕድን ምርት ፈቃዶች ናቸው፡፡ በሥራ ላይ ያሉ ባለፈቃድ ኩባንያዎች ብዛት 164 ነው፡፡ የአገር ውስጥ ባለፈቃዶች 60፣ የውጭ አገር ባለፈቃዶች 68፣ እንዲሁም የጋራ ሽርክና ባለፈቃዶች 36 ናቸው፡፡
ከማዕድናት የውጭ ንግድ ከ600 ሚሊዮን ዶላር በላይ የሚገኝ ሲሆን፣ ሁለት ሦስተኛው ከባህላዊ ወርቅ አምራቾች የሚገኝ ነው፡፡ እ.ኤ.አ. በ2024 ከማዕድን ዘርፍ ሁለት ቢሊዮን ዶላር ለማግኘት የታቀደ ሲሆን፣ ዘርፉ ለ8,000 ዜጐች የሥራ ዕድል እንደሚፈጥር ይገመታል፡፡
ይህ በእንዲህ እንዳለ የተለያዩ ኩባንያዎች በማዕድን ሚኒስቴር የፈቃድ አሰጣጥ ሒደት ላይ ቅሬታ እያቀረቡ ነው፡፡ ቅሬታ አቅራቢዎቹ ከተለያዩ አገሮች የመጡ ኩባንያዎች ሲሆኑ፣ የማዕድን ፍለጋ ፈቃድ ማመልከቻ አስገብተው ረጅም ጊዜ ቢጠብቁም ከሚኒስቴሩ ምላሽ አላገኘንም ይላሉ፡፡ አንድ የውጭ ኩባንያ ኃላፊ ለሪፖርተር እንደገለጹት፣ ማመልከቻ ካስገቡ ሦስት ዓመት ቢሆናቸው ከማዕድን ሥራዎች ፈቃድ አስተዳደር ዳይሬክቶሬት ምላሽ አላገኙም፡፡ ሌሎች ኩባንያዎች በበኩላቸው ያቀረቡዋቸው ማመልከቻዎች አሳማኝ ባልሆኑ ምክንያቶች ተቀባይነት አላገኙም ብለዋል፡፡
የችግሩ መንስዔ በቅርብ የወጣው የማዕድን ምርመራ ሥራዎች የፈቃድ ጥያቄ ማመልከቻዎች የሚስተናገዱበት መመርያ ቁጥር 02/2006 ነው፡፡ የአዲሱ መመርያ ዓላማ የማዕድን ምርመራ ፈቃድ ወስደው የማይሠሩ ግለሰቦችና ኩባንያዎችን ፈቃድ እንዳያገኙ ለመከላከል የወጣ ሕግ እንደሆነ የማዕድን ሚኒስቴር ኃላፊዎች ያስረዳሉ፡፡
በአዲሱ መመርያ መሥፈርት አንድ የማዕድን ፈቃድ ጠያቂ ፈቃድ ለማግኘት ያቀረበው ማመልከቻና የቀደምት ልምዱ ታይቶ ከመቶ 75 ነጥብ ማግኘት ይገባዋል፡፡ በድርጅቱ ቀደምት ልምድ 35 ነጥብ ይሰጠዋል፡፡ ለጉዳዩ ቅርበት ያላቸው ምንጮች እንደሚሉት ብዙዎቹ የኢትዮጵያን የንግድ ሕግ በመጠቀም አዲስ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማኅበር ኩባንያ መሥርተዋል፡፡ ‹‹በጊዜውም ለአዲስ ኩባንያ ፈቃድ አይሰጥም ያለ አካል አልነበረም፡፡ ነገር ግን በአዲሱ መመርያ መሠረት አዲስ ኩባንያ ፈቃድ አይሰጥም፡፡ በዚህና በሌሎች አሳማኝ ባልሆኑ ምክንያቶች በርካታ ኩባንያዎች ፈቃድ ተከልክለው ገንዘባቸውን ይዘው ወደ ሌሎች የአፍሪካ አገሮች ለመሄድ በዝግጅት ላይ ናቸው፤›› ብለዋል ምንጮች፡፡ የማዕድን ሚኒስቴር ኃላፊዎች ይህን ክስ ያስተባብላሉ፡፡ የሚኒስቴሩ አንድ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊ ለሪፖርተር እንደገለጹት ቀደም ሲል የነበረው የፈቃድ አሰጣጥ ሒደት ቀለል ያለ በመሆኑ፣ በርካታ ኩባንያዎች ለማዕድን ፍለጋ ሥራ የሚያስፈልገው እውቀትና ገንዘብ ሳይኖራቸው የማዕድን ፍለጋ ፈቃዶች በእጃቸው አስገብተዋል፡፡
‹‹አብዛኞቹ ኩባንያዎች የማዕድን ፍለጋ ቦታዎችን የሚነግዱ ደላላ ኩባንያዎች ናቸው፡፡ አንዳንዶቹ ፈቃድ ወስደው ምንም ዓይነት ሥራ ሳይሠሩ አሳልፈው ይሸጣሉ፡፡ ሌሎቹ ደግሞ በተሰጣቸው የማዕድን ፍለጋ ቦታዎች ሥራ ሳይሠሩ መሬቱን ታቅፈው ለረጅም ጊዜ ይቀመጣሉ፡፡ ዕርምጃውን የወሰድነው ተገቢውን ጥናት ካደረግን በኋላ ነው፤›› ያሉት ኃላፊው፣ ‹‹እነዚህን ደላላ ኩባንያዎች ለመከላከል አዲስ መመርያ ማውጣት አስፈላጊ ሆኗል፡፡ የማዕድን ፍለጋ ልምድ ያለውና አስፈላጊው ካፒታል ላላቸው ኩባንያዎች አሁንም ቢሆን ፈቃድ እንሰጣለን፤›› ብለዋል ኃላፊው፡፡
የዓለም ባንክ በኢትዮጵያ የማዕድን ዘርፍ ላይ በቅርቡ ባካሄደው ጥናት የማዕድን ሚኒስቴር ያሉበትን ችግሮች ነቅሶ አውጥቷል፡፡ ባለፈው ጥቅምት ወር በአዲስ አበባ ሒልተን የማዕድን ሚኒስቴር ኃላፊዎች ባሉበት ይፋ የሆነው ሪፖርት ሚኒስቴሩ የባለሙያ እጥረት እንዳለበት የገለጸ ሲሆን፣ የማዕድን ፈቃድ አሰጣጥ ሒደቱንም ተችቷል፡፡
‹‹በአሁኑ ወቅት የፍለጋ ፈቃድ ማመልከቻዎችን በመገምገም ረገድ ከፍ ያለ ክምችት ይታያል፡፡ መነሻ ላይ የነበረው ሐሳብ ግን ማመልከቻዎችን በየወሩ ለማየት ነበር፡፡ ይህ የሆነው በከፊል ማዕድን ይገኝባቸዋል ተብለው የሚታሰቡ ቦታዎችን ለመያዝ ብቻ ተብለው የሚቀርቡ ማመልከቻዎችንና ወይም አስፈላጊ እውቀትና ግብዓት የሌላቸውን ድርጅቶችን ለመግታት ታስቦ ሊሆን ይችላል፡፡ ቢሆንም ግን ማመልከቻዎችን በየጊዜው ለመገምገም ጉዳዩ የሚመለከተው የመንግሥት ተቋም ከባድ የአቅም ተግዳሮት እንዳለበት ግልጽ ነው፤›› ይላል ሪፖርቱ፡፡
የማዕድን ሚኒስቴር በ2005 ዓ.ም. ሥራ ላይ ያዋለው ኮምፒዩተራይዝድ የማዕድን ልማት ካዳስተር ሥራ መቋረጡ፣ በማዕድን ፈቃድ አሠራር ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ ማሳደሩን የዓለም ባንክ ጠቅሷል፡፡
Click here to claim your Sponsored Listing.
Category
Contact the hotel
Telephone
Website
Address
22 Mazoriya
Addis Ababa
28188/1000