Ethio Inform

Ethio Inform

Share

01/10/2021

አሁን የሚካሄደው የመንግሥት ምሥረታ ኢትዮጵያ ካለችበት
ችግር ለመውጣት የሚያግዝ ነው፦ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ
*************
አሁን የሚካሄደው የመንግሥት ምሥረታ ኢትዮጵያ ካለችበት
ችግር ለመውጣት የሚያግዝ መሆኑን የኢትዮጵያ ዜጎች
ለማኅበራዊ ፍትሕ /ኢዜማ/ መሪ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ተናገሩ።
ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ከኢቲቪ ጋር በነበራቸው ቆይታ አዲስ
በሚመሠረተው መንግሥት ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች ተሳትፎ
እንዲኖራቸው በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ከብልጽግና ፓርቲ ጋር
ምክክር መጀመሩን ገልጸዋል።
የተወሰኑ የተፎካካሪ ፖለቲካ ፓርቲዎች በፓርላማ ወንበር
ማግኘታቸውም የተለያዩ ሐሳቦች እንዲንሸራሸሩ ዕድል የሚፈጥር
መሆኑን ነው የተናገሩት።
በቀጣይ ሀገሪቷ አሁን ካለችበት ችግር እንድትወጣ መንግሥት
የሚመሠርተው ፓርቲ እና ተፎካካሪ ፓርቲዎች ሕዝብን ያስቀደመ
ኃላፊነት እንዳለባቸው የኢዜማ መሪ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ
ገልጸዋል።
Ebc

Want your school to be the top-listed School/college in Addis Ababa?
Click here to claim your Sponsored Listing.

Website

Address


Addis Ababa