Axis Law
17/08/2024
ይርጋ ወይም የመብት መጠየቂያ የጊዜ ገደብ [𝙋𝙚𝙧𝙞𝙤𝙙 𝙤𝙛 𝙇𝙞𝙢𝙞𝙩𝙖𝙩𝙞𝙤𝙣]
ይርጋ ማለት አንድ መብቱ ወይንም ጥቅሙ የተነካበት ሰው ይህን ጥያቄውን ስልጣን ባለው ፍ/ቤት ማቅረብ የሚችልበት በህግ ተለይቶ የተቀመጠ የጊዜ ገደብ ነው፡፡ ይህም ከሳሽ በተገቢ ትጋት መብቱን እንዲጠይቅ ለማስቻል፣ ተከሳሽ ከጊዜ ርዝመት የተነሳ የቀረበበትን ክስ ለመከላከል የሚያስችሉ ማስረጃዎችን እንዳያጣ ለማድረግ፣ እንዲሁም ከቅን ልቦና ዉጪ የሚቀርቡ ክሶችን ለማስቀረት ህጉ ያስቀመጠው መፍትሔ ነው። ለማሳያ ያክል ከብዙ በጥቂቱ በፍትሐ ብሄር ህጋችን እንዲሁም በሌሎች ህጎች የተቀመጡ የጊዜ ገደቦች እንመለከት፤
ውልን መሰረት ያደረገ ክስ በ 10 ዓመት ውስጥ፤ ከውል ዉጪ የሚመጭ ሃላፊነትን መሰረት ያደረገ ክስ በ 2 ዓመት ውስጥ፤ ውርስን መሰረት ያደረገ ክስ ክሱ በወራሾች መሀከል ከሆነ በ 3 ዓመት ዉስጥ፤ ውርሱ ሲከፈት ከሳሽ በመብቱ ሊሰራበት የማይችል ከነበረ በመብቱ መስራት ከቻለበት ጊዜ አንስቶ በ15 አመት ዉስጥ፤ ክርክሩ ወራሽ በሆነና ባልሆነ ሰው የሆነ እንደሆነ በ10 አመት ዉስጥ፤ ንብረትን መሰረት ያደረገ ክስ ማለትም ንብረቱ የተወሰደበት ወይንም በይዞታው ላይ ሁከት የተፈጠረበት ሰው በ2 ዓመት ዉስጥ፤ በአሰሪና ሰራተኛ ጉዳይ የስራ ውሉ ያለአግባብ ተቋርጧል በሚል የሚቀርብ ክስ ውሉ በተቋረጠ በ3 ወር ዉሰጥ፤ የደሞዝ የትርፍ ሰአት እንዲሁም ሌሎች ክፍያን የተመለከቱ ጉዳዮች በ6 ወራት ዉሰጥ፤ የስራ ውል መቋረጥ በተመለከተ የሚቀርብ ማንኛውም ጥያቄ በ6 ወራት ዉሰጥ መቅረብ ይኖርበታል፡፡
ለመሆኑ በይርጋ ቀሪ የማይሆኑ መብቶች ይኖሩ ይሆን?
https://t.me/MrYenesewD/172
11/08/2024
አባትነትን በፍርድ ውሳኔ ከማረጋገጥ ጋር በተገናኘ በሚቀርብ አቤቱታ እና ክርክር ወቅት የዲ.ኤን.ኤ (DNA) ምርመራ እንዲደረግለት በመጠየቅ ክርክር የሚያቀርብ ተከራካሪ፣ ለዚሁ የህክምና ምርመራ የሚያስፈልገውን ወጪ የመሸፈን ግዴታ ይኖርበታል። ዲ.ኤን.ኤ ምርመራን እንደማስረጃ የቆጠረ ተከራካሪ ማስረጃው በእኔ ቢቆጠርም ወጪውን መሸፈን ስለማልችል ምርመራው መደረግ ያለበት በሌላኛው(ዲ.ኤን.ኤ ምርመራን ባልጠየቀው) ተከራካሪ ወጪ ነው የሚል ክርክር ከመሰረታዊ የማስረጃ ህግ መርህ የሚቃረን ነው። የዲ.ኤን.ኤ (DNA) ምርመራ የህክምና ዘዴን (ሳይንስን) መሰረት በማድረግ የሚከናወን በመሆኑ በማስረጃ ዝርዝር ተካቶ ከሆነ በቂ እና ህጋዊ ምክንያት ከሌለ በስተቀር ሳይሰማ ሊታለፍ አይገባም።
https://t.me/MrYenesewD
Mr. Yenesew |አቶ የኔሰው Legal Service | ህግ አገልግሎት
Click here to claim your Sponsored Listing.
Contact the business
Telephone
Website
Address
Bole Medhanialem Church, Abrhams Building, 5th Floor
Addis Ababa
Opening Hours
| Monday | 08:30 - 16:00 |
| Tuesday | 08:30 - 04:00 |
| Wednesday | 08:30 - 16:00 |
| Thursday | 08:30 - 16:00 |
| Friday | 08:30 - 16:00 |
| Saturday | 09:00 - 15:00 |