MFM

MFM

Share

31/05/2026

በባህረ ሰላጤው ሀገራት መካከል ያለው የከረረ ዲፕሎማሲያዊ ፍጥጫ! 🇸🇦🤝🇦🇪

-NEWS | አለም አቀፍ ትንታኔ በ Mohammed Miftah Derb

የመካከለኛው ምስራቅ የፖለቲካ ውጥረት አዲስ ምዕራፍ ይዟል። ሳዑዲ አረቢያ በተባበሩት አረብ ኤምሬትስ (UAE) አካሄድ ላይ ያላትን ከፍተኛ ቅሬታ ለዋሽንግተን በምስጢር ማድረሷን የዎል ስትሪት ጆርናል (WSJ) ዘገበ።

ምን ተፈጠረ?
ኢማሬትስ በኢራን የነዳጅ ማጣሪያዎች (በባንደር አባስ እና አሳሉዬህ) ላይ ያደረሰችውን ተደጋጋሚ የአየር ጥቃት ተከትሎ፣ ሳዑዲ አረቢያ ከፍተኛ ስጋት ውስጥ መግባቷ ተሰምቷል። ሪ ያድ “የኢማሬትስ እርምጃ ኢራን በባህረ ሰላጤው የነዳጅ መሰረተ ልማቶች ላይ የአጸፋ ጥቃት እንድትሰነዝር መንገድ ይከፍታል፣ የነዳጅ ዋጋንም እንዲንር ያደርጋል” ስትል ነው ለዩናይትድ ስቴትስ አቤቱታዋን ያቀረበችው።

የሳዑዲ ፍላጎት ምንድን ነው?
ሳዑዲ አረቢያ ዋሽንግተን በአቡ ዳቢ ላይ ጫና እንድታደርግ እና ወታደራዊ እርምጃዎች ቆመው ወደ ዲፕሎማሲያዊ ውይይት እንዲመለሱ አጥብቃ አሳስባለች።

📌 የእርስዎ አስተያየት ምንድን ነው?
ይህ የሳዑዲ አረቢያ ስጋት የባህረ ሰላጤውን ጥምረት ያናጋው ይሆን? ወይስ ቀጠናው ወደ ከፋ የነዳጅ ዘይት ጦርነት እያመራ ነው? ሃሳብዎን በኮሜንት ያጋሩን።

መረጃዎች በፍጥነትጰእንዲደርሷችሁ የቴሌግራም ቻናላችንን ይከተሉ
https://t.me/mekaneselamfm

Want your business to be the top-listed Media Company in Addis Ababa?
Click here to claim your Sponsored Listing.

Telephone

Website

Address


Addis Ababa
KELIFFABUSSINESCENTER