Excellency Today Media

Excellency Today Media

Share

08/03/2022

በካርኪቭ አቅራቢያ በተካሄደ ጦርነት የሩሲያ ጦር ከፍተኛ አዛዥ መገደላቸውን የዩክሬን ጦር የስለላ አገልግሎት አስታወቀ።

ቢቢሲ ጉዳዩን ከገለልተኛ ወገን ማረጋገጥ ያልቻለ ሲሆን የሩሲያ ባለስልጣናትም በጉዳዩ ዙሪያ አስተያየት አልሰጡም።

የዩክሬን መከላከያ ሚኒስቴር ባወጣው መግለጫ መሠረት ቪታሊ ጌራሲሞቭ፤የሜጀር ጄኔራል ማዕረፍ ያላቸው ሲሆንየ41ኛው የሩሲያ ማዕከላዊ ዕዝ ምክትል ዋና አዛዥ ነበሩ።

በርካታ ከፍተኛ የሩሲያ የጦር መኮንኖችም መገደላቸውን እና ቀሪዎቹም መቁሰላቸውን ገልጿል ይሄው የዩክሬን ተቋም።

የዩክሬን የስለላ ድርጅት እንዳስታወቀው ጌራሲሞቭ በሁለተኛው የቺቺን ጦርነት እና በሶሪያ የሩሲያ ወታደራዊ ዘመቻ ወቅት መሳተፋቸውን ገልጿል። "ክራይሚያን ለመመለስ" ባደረጉት አስተዋጽኦም ሜዳልያ አግኝተዋል።

የዩክሬን ባለስልጣናት የጌራሲሞቭ ነው ያሉትን ፎቶ በትዊተር ይፋ ያደረጉ ሲሆን “ተወግዷል” የሚለው ቃል ከስሩ በቀይ ቀለም አስፍረዋል።

08/04/2021

የአውሮፓ መድኃኒት ተቆጣጣሪ መስሪያ ቤት ለኮቪድ-19 መከላከል አስትራዜኒካ ክትባትን የሚወስዱ ሰዎች በደም መርጋት የመጠቃታቸው እድል እጅጉን አናሳ ነው ሲል ገለፀ።

በአውሮፓ የተከሰቱ በርካታ የደም መርጋቶችን የመረመረው የአውሮፓ መድኃኒቶች ኤጀንሲ፣ ክትባቱ ከሚያስከትለው ጉዳት ይልቅ ጥቅሙ የላቀ ነው ሲል ተናግሯል።

አስትራዜኒካን የወሰዱ ሰዎች በቀጥታ በደም መርጋት ይጠቃሉ የሚለውን ለማረጋገጥ የሚያስችል ፍንጭ አላገኘሁም ያለው ኤጀንሲው፤ አብዛኞቹ የተመዘገቡት ክስተቶች እድሜያቸው ከ60 በታች በሆኑ ሴቶች ላይ ሲሆን የተወሰኑ ወንዶችም ችግሩ ገጥሟቸዋል ሲል አብራርቷል።

ኤጀንሲው 86 የደም መርጋት የገጠማቸውን ህሙማን ጉዳይ መርምሯል።

የአውሮፓ ሕብረት ከ20 ሚሊዮን በላይ ሰዎችን የአስትራዜኒካ ክትባት መውሰዳቸው ተገልጿል።

08/04/2021

ለንደን የሚገኙት የምያንማር አምባሳደር ወደ ኤምባሲው ቅጥር ግቢ እንዳይገቡ መደረጋቸውን ገለፁ።

አምባሳደሩ ኪያው ዝዋር ሚን እምዳሉት የምያንማር ወታደራዊ አታሼ የኤምባሲውን ሠራተኞች ቢሯቸውን ለቅቀው እንዲወጡ ካደረገ በኋላ እሳቸውንም ከአሁን በኋላ የአገሪቷ ወኪል አለመሆናቸውን ገልጾላቸዋል።

አምባሳደሩ ለሮይተርስ የዜና ወኪል " ከግቢው አስወጥተው ቆልፈውብኛል" ብለዋል።

የምያንማር ወታደራዊ ኃይል በመፈንቅለ መንግሥት ስልጣን የያዘው በፈረንጆቹ የካቲት 1/2021 የነበረ ሲሆን ይህም ለሳምንታት የዘለቀ ተቃውሞና አመጽ አስከትሏል።

Want your organization to be the top-listed Government Service in Addis Ababa?
Click here to claim your Sponsored Listing.

Category

Telephone

Website

Address


Addis Ababa