Mahlet Getachew Sermon
በራስህ ባርከኝ🙏
ራስህን ገለል አርገህ ከምትሰጠኝ ከምትመልስልኝ ጥያቄ ጠብቀኝ!!!
በራስህ ባርከኝ ባንተ መኖር።
ሕያው እንጀራ::
አባቶች ከሰማይ በወረደው እንጀራ(መና) የምድር ሕይወታቸውን አስቀጥለው ቢሆንም ነገር ግን ሞተዋል ።
እግዚአብሔር የሰጠው እንጀራ እርሱ ከሰማይ የወረደው ለዓለም እንካችሁ ያለው እንጀራ እርሱ ሕይወት ነው የምድሩን ብቻ ሳይሆን የሰማዩን ሕይወት የምትቀጥልበትን እስትንፋስ በእርሱ በማመን ተገኝቷል
ይሄ እንጀራ ሕያው እንጀራ ይባላል እርሱም እየሱስ ክርስቶስ ነው ይህን እንጀራ የበላ ለዘላለም አይራብም በእየሱስ የሚያምንም ከቶ አይጠማም።
ዮሐንስ 6 (አዲሱ መ.ት)
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
⁴⁷ እውነት እላችኋለሁ፤ የሚያምን ሁሉ የዘላለም ሕይወት አለው።
⁴⁸ የሕይወት እንጀራ እኔ ነኝ።
⁴⁹ አባቶቻችሁ በምድረ በዳ መና በሉ፤ ይሁን እንጂ ሞቱ።
⁵⁰ ነገር ግን ሰው እንዳይሞት ይበላው ዘንድ ከሰማይ የሚወርድ እንጀራ ይህ ነው።
⁵¹ ከሰማይ የወረደ ሕያው እንጀራ እኔ ነኝ፤ ማንም ሰው ከዚህ እንጀራ ቢበላ ለዘላለም ይኖራል፤ ይህም እንጀራ፣ ለዓለም ሕይወት እንዲሆን የምሰጠው ሥጋዬ ነው።”
Click here to claim your Sponsored Listing.
Category
Website
Address
Addis Ababa
15/05/2022