Sinte tek

Sinte tek

Share

08/05/2020

ፍቅር ፈራን
"ፈራን"
ፍቅርን ፈራን መቀራረብ ፈራን
እንዳልተዛመድን እንዳልተዋለድን
ፈርተን መዋደድን ጉርብትናን ናድን
እኛነትን ትተን እኔነትን ለመድን
"ፈራን"
ፍቅርን ፈራን ጥላቻን ሰራን ብቸኝነት ጠራን
በጋራ ቤታችን አጥር ድንበር ሰራን
"ናቅን"
በልዩነት ደምቀን ያልኖርን ያህል አንድም ቀን
እልህ ተናነቅን
"ናቅን"
መቻቻልን ናቅን ለፀብ አሟሟቅን
ለአመፅ ስንነሳ ለሰላም ወደቅን
አገር ስትቃጠል ከዳር ሆነን ሞቅን
"ጠላን"
መወያየት ጠላን መነጋገር ጠላን
መደማመጥ ጠፍቶ መነቋቆር በዝቶ
መናናቅ በርክቶ
መመካከርን ስንረሳ መከባበርን ስንረሳ
እጃችን በወንድማችን ላይ ዱላ አነሳ
የቃየል ምቀኝነት በልባችን ላይ ነግሳ
"ራቅን"
የተስፋ ሻማችን ተለኩሶ
ወጋገኑ መታየት ሲጀምር አድማሱን ጥሶ
እኛ ግን ራቅን ብሩህ ነገን ራቅን
ዛሬን ተጣበቅን ትላንትን ናፈቅን
========//==========
ሎሬት ፀጋዬ ገ/መድህን

08/05/2020

‹‹……………ተው ብዬህ አልነበረም?......ክፉ ቀን ማለፊያ
ጥበብን አልገርሁህም ነበር?.........ክፉ ቀንን በጥበብ
ከማለፍ በላይ ጥበብ የለም! ይች ደም መላስ የለመደች
ሀገር የምትለወጥ መስሎሃል!
#ቴዎድሮስን በላች፣ አልተለወጠችም፡፡
#ገብርዬን በላች፣ አልተለወጠችም፡፡
#ሚኒሊክ ደከመላት፣ አልተለወጠችም፡፡
#ፋሲልን በላች፣ አልተለወጠችም፡፡
#አሉላን በላች፣ አልተለወጠችም፡፡
#አንተንም በላች፣ አልተለወጠችም፡፡
#የበላይን ደም ጠጣች፣ ይኸው አልተለወጠችም፡፡
ስንት ጀግኖች ሞቱላት፣ አ ል ተ ለ ወ ጠ ች ም፡፡
አልነገርኩህም?….አልነገርኩህም?…አልነገርኩህም?
አትሰማም! አትሰማማ!
ተው እያልኩህ ሞትህ!......ሞ ት ህ!
…….>>

Want your organization to be the top-listed Government Service in Addis Ababa?
Click here to claim your Sponsored Listing.

Category

Website

Address


Addis Abeba
Addis Ababa