Abay Media Network
14/06/2025
እስራኤል ሌላ ዙር ጥቃት ፈፀመች !
ቴላቪቭ በርካታ ፍንዳታዎችን እና ውድመትን ያስከተለው ጥቃት በኢራን ላይ መፈፀሟ ተነገረ ።
በቴህራን የኢራን መንግስት ቲቪ እንደዘገበው ከሆነ ዛሬ አመሻሹ ላይ እስራኤል ከ150 በላይ ቦታዎች ላይ ጥቃት መፈፀሟን እና በተፈፀመው ጥቃትም በኢራን ደቡባዊ ቡሻህር ግዛት ውስጥ ከጋዝ ማውጫ ጨምሮ በርካታ ቦታዎች ላይ ጉዳት መድረሱን የገለፀ ሲሆን
በጥቂቱም 20 ህጻናትን ጨምሮ ወደ 60 የሚጠጉ ሰዎች መገደላቸውን እና በመላ ሀገሪቱ ተጨማሪ ጥቃቶች መፈፀሙን ዘግቧል ። ተብሏል
በማህበራዊ ሚዲያ ላይ እየተሰራጨ ያለው እና በሲኤንኤን የተወሰደው የቪዲዮ ምስል በኢራን ደቡባዊ ቡሻህር ግዛት ውስጥ ከጋዝ ማውጫው የተነሳ ከፍተኛ የእሳት ቃጠሎ እና ጭስ የሚያሳይ ሲሆን ጥቃቱ ከእስካሁኑ የከፋ መሆኑን የዘገበው ሮይተርስ ነዉ
Want your public figure to be the top-listed Public Figure in Addis Ababa?
Click here to claim your Sponsored Listing.
Click here to claim your Sponsored Listing.
Category
Telephone
Website
Address
4 Kilo
Addis Ababa