Dymans-Eth

Dymans-Eth

Share

12/11/2020

የሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት ባካሄደው 4ኛ መደበኛ ስብሰባው ላይ 'በወንጀል የተጠረጠሩ' የምክር ቤት አባላትን ያለመከሰስ መብት ማንሳቱን አሳወቀ።

በዚህም መሰረት፦

- ዶክተር ደብረጸዮን ገብረሚካኤል
- አቶ አስመላሽ ወልደሰንብት
- አቶ አባይ ፀሃዬ
- ዶክተር አምባሳደር አዲስ ዓለም ቤሌማ
- አቶ ጌታቸው ረዳ
- አቶ አፅበሃ አረጋዊ
- አቶ ገብር እግዚአብሄር አርአያ ጨምሮ ሌሎችን ግለሰቦችን ያለመከሰስ መብታቸውን ምክር ቤቱ አንስቷል።

ግለሰቦቹ የተጠረጠሩባቸው ወንጀሎች የጦር መሳሪያ ይዞ በማመፅ ፣ የሀገር መከላከያን በመውጋትና በሌሎች ተያያዥ ወንጀሎች ዋና አድራጊነት ነው ተብሏል።

በሌላ በኩል፦

የህ/ተ/ም/ቤት አቶ ፍቅሩ ገ/ሕይወትን የምርጫ ቦርድ አባል አድርጎ ሾሟል። (ኢቲቪ-HoPR)

DYMANS - ETH

Photos 11/04/2020

የኮቪድ-19 ወረርሽኝ ስርጭትን ለመከላከል፣ ለመቆጣጠርና የሚያስከትለውን ጉዳት ለመቀነስ የወጣው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ማስፈፀሚያ ደንብን የፌዴራል ጠቅላይ አቃቤ ህግ ይፋ አደረገ።

ክልከላን በሚመለከት፦

- ማንኛውም ሃይማኖታዊ ይሁን ፖለቲካዊ ስብሰባዎች፣ እድር፣ ደቦ፣ እቁብና ሌሎችም ከ4 ሰው በላይ ስብሰባዎች ክልክል ናቸው።

-አራት ሰዎችም ቢሆኑ ሁለት የአዋቂ ሰው እርምጃ የጠበቀ መሆን አለበት።

- ቀብርና ሌሎች አስፈላጊ ጉዳዮች ሲኖሩ ግን እየታዩ ሊፈቀዱ የሚችሉበት አሰራር ይኖራል።

- ታራሚዎች ከጠበቆቻቸው ጋር አስፈላጊው ጥንቃቄ ተደርጎ እንዲገናኙ የሚፈቀድ ቢሆንም ጥየቃ ለሚሄዱ ሰዎች አይፈቀደም።

- በፖሊስ የተያዙ እስረኞችንም ስንቅ ከማቀበል በስተቀር መገናኘት የተከለከለ ነው።

- በድንበር አካባቢ ከካርጎ፣ የደረቅና ፈሳሽ ጭነት አገልግሎቶች በስተቀር ሌሎች እንቅስቃሴዎች ዝግ ተደርገዋል።

- የቤት ተከራዮች በራሳቸው ፍላጎት ካልወጡ በስተቀር ማስወጣትና ኪራይም መጨመር በአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ተከልክሏል።

- ሰራተኞችን መቀነስና የስራ ቅጥር ውል ማቋረጥም ተከልክሏል።

- ተማሪዎችና መምህራን በኦን ላይን ካልሆነ በአካል እንዲገናኙ አይፈቀድም።

Want your business to be the top-listed Advertising & Marketing Company in Addis Ababa?
Click here to claim your Sponsored Listing.

Website

Address


Addis Ababa