Wollo Times
04/05/2026
ፓኪስታን በአሜሪካ ቁጥጥር ስር የነበሩ የኢራን መርከበኞችን ልታስረክብ ነው
ፓኪስታን በአሜሪካ ቁጥጥር ስር የነበሩ 22 የኢራን መርከበኞችን ለቴህራን ልታስረክብ ነው
ፓኪስታን በአሜሪካ ጦር ተይዘው የነበረ የአንድ የኢራን መርከብ 22 አባላትን ዛሬ ሰኞ ለቴህራን እንደምታስረክብ አረጋግጣለች።
የእስላማባድ ባለስልጣናት ይህንን ውሳኔ "የመተማመን መገንቢያ እርምጃ" ሲሉ የገለጹት ሲሆን፤ ይህም በሆርሙዝ የባህር ወሽመጥ አካባቢ ያለውን ከፍተኛ ውጥረት ለማርገብ ያለመ መሆኑ ተገልጿል።
መርከበኞቹ በአሜሪካ የባህር ኃይል ቁጥጥር ስር ከዋሉ በኋላ በፓኪስታን በኩል አልፈው ወደ ሀገራቸው እንዲመለሱ ስምምነት ላይ ተደርሷል።
ይህ የፓኪስታን እርምጃ በቅርቡ በሆርሙዝ የባህር ወሽመጥ ላይ በተፈጠረው ወታደራዊ እና ዲፕሎማሲያዊ ፍጥጫ ሳቢያ በኢራን እና በምዕራባውያን ሀገራት መካከል የሻከረውን ግንኙነት ለማለስለስ የሚረዳ ዲፕሎማሲያዊ ጥረት ተደርጎ ተወስዷል።
ርክክቡ ዛሬ ሰኞ እለት እንደሚከናወን የሚጠበቅ ሲሆን፤ እስላማባድ በቀጣናው ሰላምና መረጋጋት እንዲሰፍን ያላትን ፍላጎት የምታሳይበት እንደሆነም አስታውቃለች መባሉን የዘገበው አናዶሉ ነው።
Wollo Times
https://www.facebook.com/wollotimes12
30/04/2026
ሰበር ኢራን የአሜሪካን እገዳ በወታደራዊ ኃይል ታነሳለች።
የቀድሞው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር #ሞታኪ “የባህር ኃይል እገዳ ማለት የጦርነት አዋጅ ማለት ነው” ብለዋል።
የቀድሞው የውጭ ጉዳይ ሚኒስት ሞታኪ“ #ተዋጊዎቻችን ነገ ወይም በሚቀጥለው ሳምንት እርምጃ ሊወስዱ ይችላሉ።” ብለዋል ።
Wollo Times
https://www.facebook.com/wollotimes12
29/04/2026
ሰበር ሰበር 52 የኢራን መርከቦች እገዳውን ጥሰው አለፉ‼️
የትራምፕ እገዳ የት ነው ?
ባለፉት 72 ሰዓታት ውስጥ ብቻ 52 የኢራን መርከቦች ዩናይትድ ስቴትስ በኢራን የውሃ ክልል ላይ የጣለችውን እገዳ ጥሰው ማለፋቸውን የኢራን ፋርስ የዜና ወኪል ዘግቧል።
እስከ ሰኞ ምሽት 4፡00 ሰዓት በአካባቢው አቆጣጠር ያለውን የሳተላይት መከታተያ መረጃ ጠቅሶ የወጣው ዘገባ እንደሚያመለክተው መስመሩን ካለፉት መርከቦች መካከል 31ዱ የነዳጅ ጫኝ መርከቦች ሲሆኑ 21ዱ ደግሞ የጭነት መርከቦች ናቸው።
Wollo Times
https://www.facebook.com/wollotimes12
Click here to claim your Sponsored Listing.
Category
Contact the business
Telephone
Website
Address
America
Addis Ababa