Kumneger

Kumneger

Share

03/04/2026
20/03/2026

እነዚህ ዝርያቸው እየተመናመነ ያለው ኖርዘርን ዋይት ራይኖ በአሁኑ ወቅት ብዛታቸው ሁለት ብቻ ሲሆን ከማንኛውም አደን ለመጠበቅ ሲባል 24 ሰአት በጠባቂዎች ይጠበቃሉ!

15/03/2026

ኢራን የሆርሙዝ የባህር ስርጥ የተዘጋው "ለጠላቶቿና ለባልደረቦቻቸው" መሆኑን አስታወቀች
የኢራን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አባስ አራቅቺ፤ ስልታዊ ጠቀሜታ ያለው የሆርሙዝ የባህር ስርጥ ክፍት ቢሆንም፣ "ለኢራን ጠላቶችና ለባልደረቦቻቸው" ግን ዝግ መሆኑን ገለጹ።
ሚኒስትሩ ዛሬ በሰጡት መግለጫ፤ የባህር ስርጡ ለዓለም አቀፍ የንግድ መርከቦች ዝውውር ክፍት ሆኖ እንደሚቆይ ጠቁመው፣ ነገር ግን ከኢራን ጋር ግጭት ውስጥ ላሉ ወገኖችና ለደጋፊዎቻቸው የነዳጅ ጫኝ መርከቦችም ሆኑ ሌሎች የንግድ መርከቦች ማለፊያ እንደማይሆን በግልጽ አስታውቀዋል።
ይህ የአባስ አራቅቺ መግለጫ የወጣው በኢራን፣ በእስራኤልና በአሜሪካ መካከል ያለው ቀጠናዊ ውጥረት በከፍተኛ ሁኔታ በጨመረበትና የባህር ላይ ደህንነት ስጋት በገነነበት ወቅት ነው።

Want your public figure to be the top-listed Public Figure in Addis Ababa?
Click here to claim your Sponsored Listing.

Category

Website

Address


Addis Ababa