Global Addis Media
16/02/2026
የምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ መልዕክት
እንኳን ለረመዳን ወርኃ ጾም አደረሳችሁ!
በእስልምና የዘመን አቆጣጠር፣ ዘጠነኛው ወር የሆነው ረመዳን የተቀደሰ ወር ነው። ጾም፣ ዱአ እና በጎ ሥራ ይከናወንበታል።
ጾም ራስን ማስገዣ መሣሪያ ነው። ከስሜታዊነት ወደ መንፈሳዊነት ያሻግረናል። ዱአ ከፈጣሪ ጋር መገናኛ መንገድ ነው። በጎ ሥራ ማኅበረሰብን በማገልገል ሰማያዊ ዋጋ የሚገኝበት ዕድል ነው።
ቅዱስ ቁርአን በወረደበት በዚህ የተቀደሰ ወር፣ ሀገራችንንና ወገናችንን እያሰብን፣ የተቀደሱ ተግባራትን ተግተን እንድንፈጽም አደራ አለብን።
የምንጠቀምበት የረመዳን ወር ይሁንልን።
Want your business to be the top-listed Media Company in Addis Ababa?
Click here to claim your Sponsored Listing.
Click here to claim your Sponsored Listing.
Category
Contact the business
Telephone
Website
Address
Addis Ababa