Global Addis Media

Global Addis Media

Share

16/02/2026

የምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ መልዕክት

እንኳን ለረመዳን ወርኃ ጾም አደረሳችሁ!

በእስልምና የዘመን አቆጣጠር፣ ዘጠነኛው ወር የሆነው ረመዳን የተቀደሰ ወር ነው። ጾም፣ ዱአ እና በጎ ሥራ ይከናወንበታል።

ጾም ራስን ማስገዣ መሣሪያ ነው። ከስሜታዊነት ወደ መንፈሳዊነት ያሻግረናል። ዱአ ከፈጣሪ ጋር መገናኛ መንገድ ነው። በጎ ሥራ ማኅበረሰብን በማገልገል ሰማያዊ ዋጋ የሚገኝበት ዕድል ነው።

ቅዱስ ቁርአን በወረደበት በዚህ የተቀደሰ ወር፣ ሀገራችንንና ወገናችንን እያሰብን፣ የተቀደሱ ተግባራትን ተግተን እንድንፈጽም አደራ አለብን።

የምንጠቀምበት የረመዳን ወር ይሁንልን።

Want your business to be the top-listed Media Company in Addis Ababa?
Click here to claim your Sponsored Listing.

Telephone

Website

Address


Addis Ababa