Ethio Green Mobility Week
24/11/2025
2ኛው የኢትዮ-ግሪን ሞቢሊቲ ሳምንት ከታህሳስ 9 እስከ 12 ይካሄዳል
+++++++++++++++++
| 2ኛው የኢትዮ-ግሪን ሞቢሊቲ ሳምንት ከታህሳስ 9 እስከ 12 እንደሚካሄድ የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚንስቴር አስታወቀ።
የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚንስትር ዶክተር አለሙ ስሜ ዝግጅቱን በተመለከተ ለመገናኛ ብዙሃን በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ እንደተናገሩት፤ ግሪን ሞቢሊቱ ሳምንቱ ኢትዮጵያ በአረንጓዴ ትራንስፖርት ዘርፍ የደረሰችበትን ደረጃ የምታሳይበት ነው።
ኢትዮጵያ በአረንጓዴ ልማት ለአየር ንብረት የማይበገር ኢኮኖሚ ለመገንባት ከፍተኛ ጥረት እያደረገች ትገኛለች፤ በዚህ ሂደት የትራንስፖርት ዘርፉ የራሱን ሚና እንዲወጣ እየተሰራ ይገኛል ብለዋል።
ከትራንስፖርት ዘርፉ የሚወጣውን በካይ ጋዝ ለመቀነስና በኤሌክትሪክ ብቻ የሚሰሩ ተሽከርካሪዎችን ወደ ሀገር ውስጥ በብዛት ለማስገባት በርካታ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን አንስተዋል።
የኢትዮ ግሪን ሞቢሊት ኤግዚቢሽንና ባዛሩ ዘርፉን ለማሳደግ እየተሰሩ ያሉ ሥራዎች ለማስተዋወቅ እንደሚያግዝ ተናግረዋል።
በኤግዚቢሽኑ የኤሌክትሪክ መኪና አስመጪዎች፣ የኤሌክትሪክ መኪና ተሸከርካሪ መለዋወጫ አቅራቢዎች፣ በጋዝ የሚሰሩ ተሽከርካሪዎችን የሚመረቱና ከውጭ የሚያስገቡ የሀገር ውስጥና ዓለም አቀፍ ድርጅቶች ተሳታፊ እንደሚሆኑ ገልፀዋል።
በኤግዚቢሽኑ አምራቾች ከፖሊሲ አውጭዎች ጋር ዘርፉን ለማዘመንና ያለውን ማነቆ ለመፍታት በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ ውይይት እንደሚያደርጉ ተናግረዋል።
በአጠቃላይ በዝግጅቱ ከ100 በላይ በአረንጓዴ ትራንስፖርት ዘርፍ የተሰማሩ ዓለም አቀፍና ሀገር በቀል ተቋማት ተሳታፊ እንደሚሆኑ ጠቁመዋል።
በክብረአብ በላቸው
++++++++++++++++++
#ጋዜጣፕላስ #ኢትዮጵያ #አርንጓዴትራንስፖርት
24/11/2025
Click here to claim your Sponsored Listing.
Category
Culinary Team
Attire
Contact the business
Telephone
Website
Address
Hilton Hotel, # 335,336
Dubai