Higher Education Strategy Center

Higher Education Strategy Center

Share

24/09/2021

የትምህርት ጥራትን ለማሻሻል ከቀረቡት ረቂቅ ሰነድ

23/09/2021

የኢትዮጵያ ትምህርት ጥራት ማዕቀፍና የከፍተኛ ትምህርት እና ስልጠና የዕውቅና አሰጣጥ ስትራቴጂ ረቂቅ ሰነዶች ላይ ግምገማ ተደረገ፡፡
------------------------------------------------------------------------------------------------------------
በሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር አዘጋጅነት በአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ የትምህርት ጥራትን ለማሻሻል ከቀረቡት ረቂቅ ሰነዶች አንዱ በማዕከላችን ከፍተኛ ተመራማሪ በሆኑት ወ/ሮ አማረች ከበደ የኢትዮጵያ ትምህርት ጥራት ማዕቀፍ ረቂቅ ሰነድ የቀረበ ሲሆን የከፍተኛ ትምህርት እና ስልጠና የዕውቅና አሰጣጥ ስትራቴጂ ረቂቅ ደግሞ ደረጄ እንግዳ ዶ/ር ቀርቧል፡፡ በቀረቡ ሰነዶች ላይ ከታዳሚዎች ጠንካራ ጥያቄዎችና አስተያየቶች ተነስተዋል፡፡ ውይይቱ በነገውም ዕለት የሚቀጥ ይሆናል

21/09/2021

በሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት የአካዳሚክ ነጻነት ዙሪያ የተደረገ ውይይት

08/09/2021

እንኳን ለበዓሉ በሰላም አደረሳችሁ
አዲሱ ዓመት የሰላም የጤና የመተሳሰብ እንዲሆንላችሁ ማዕከላችን መልካም ምኞቱን ይገልጻል

Photos from Higher Education Strategy Center's post 04/09/2021

የከፍተኛ ትምህርት ስትራቴጂ ማዕከል 14 የሚደርሱ የፖሊሲ ምክረ ሃሳብ እና የማዕከሉ የውጪና የውስጥ የተገልጋይ እርካታ የዳሰሳ ጥናት ላይ ውይይት አደረገ፡፡
************************************************************************
የመርሃ ግብሩ መክፈቻ ንግግር ያደረጉት የማዕከሉ ዋና ዳይሬክተር ክቡር ዶ/ር ሃብታሙ ተካ ሲሆኑ በንግግራቸውም ማዕከሉ በበጀት ዓመቱ ያቀዳቸውን ስራዎች በወቅቱ በመጠናቀቃቸው ከዚህ በፊት እንደክፍተት ይታዩ የነበሩት የማዕከሉ ድክመቶችን መሻሻል እንደታየበት የሚያመለክቱ 14 የሚሆኑ የተጠናቀቁ የፖሊሲ ምክረ ሃሳቦች ለውይይት መቅረባቸውን በመግለጽ መድረኩን በይፋ ከፍተዋል፡፡
ማዕከሉ ነሐሴ 28 እና 29/2013ዓ.ም በአዳማ ከተማ ኤክስኪዩቲቭ ሆቴል በ2013 ዓ.ም አቅዶ ካጠናቀቃቸው ስራዎች መካከል 14 የሚሆኑ የፖሊሲ ምክረ ሃሳቦች የቀረቡ ሲሆን ጥናቶቹም፡-
1. በመውጫ ፈተና ላይ የሚስተዋሉ ችግሮችን የሚፈታ አማራጭ የፖሊሲ ምክረ ሃሳብ
2. የከፍተኛ ትምህርት ተማሪዎች ወደ ስራ ዓለም የሚሸጋገሩበትን ሁኔታ አማራጭ የፖሊሲ ምክረ ሃሳብ
3. በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የአካዳሚክ ሙስና (Academic Dishonesty) ችግሮችን ለመፍታት አማራጭ የፖሊሲ ምክረ ሃሳብ
4. በቴክኖሎጂ የተደገፈ የተከታታይ፣የርቀትና የመደበኛ ትምህርት አሰጣጥ ያለበትን ደረጃ በማጥናት አማራጭ የፖሊሲ ምክረ ሃሳብ
5. የከፍተኛ ትምህርት የአመራርና የአካዳሚክ ስታፍ ዲጂታል ቴክኖሎጂ ክህሎትን ለማሳደግ የሚያስችል መመሪያ
6. የከ/ት/ተቋማት የበጎ ፍቃድ እና ብሔራዊ አገልግሎት ተግዳሮቶችን የሚቀርፍ የፖሊሲ ምክረ ሃሳብ
7. የምርምር ዩኒቨርስቲዎችን ለማልማት የሚያስችል ፍኖተ ካርታ
8. በTVET ተቋማት ሀገር በቀል ታለንት እና ክህሎት ችግሮችን የሚፈታ አማራጭ የፖሊሲ ምክረ ሃሳብ
9. በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ሀገር በቀል እውቀት የሚለማበትና የመመራበትን ስርዓት ለመፍጠር አማራጭ የፖሊሲ ምክረ ሃሳብ
10. የምርምር ዩኒቨርስቲዎች አገር አቀፍ ስታንዳርድ
11. የ Applied & technical university አገር አቀፍ ስታንዳርድ
12. Comprehensive university አገር አቀፍ ስታንዳርድ
13. በከፍተኛ ትምህርትና ስልጠና የአደጋ ጊዜ ክስተቶች ተጽዕኖን ለመቀነስና በዘላቂነት ምላሽ ለመስጠት የሚያስችል አማራጭ የፖሊሲ ምክረ ሃሳብ
14. የሳይንሳዊ ባህል ግንባታ እና ሀገር በቀል እውቀት ተግዳሮቶች እና እድሎች ላይ አማራጭ የፖሊሲ ምክረ ሃሳብ ሲሆኑ
በመጫረሻም የማዕከሉ ዋና ዳይሬክተር ክቡር ዶ/ር ሀብታሙ ተካ እና የማዕከሉ ም/ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ተስፋዬ ሙህዬ በቀረቡት አስራ አራት ምክረ ሃሳቦች እና የማዕከሉ የውጪና የውስጥ ተገልጋይ እርካታ የዳሰሳ ጥናት ላይ ከተሳታፊዎች በተነሱ ሀሳቦች ላይም ጥልቅ ውይይት በማድረግና የተገኙ ጠቃሚ ግብኣቶች በማካተት ለቀጣይ ጥናቱ ውጤታማነት እንደሚሰራ እና የ2014 ዓ.ም ስራዎች አተገባበር ላይ አቅጣጫ በማስቀመጥ ውይይቱ ተጠናቋል፡፡

24/08/2021

የከፍተኛ ትምህርት ስትራቴጂ ማዕከል አመራርና ሰራተኞች 100% የወር ደምዛቸውን ለመስጠት እና ደም ለመለገስ በመወሰን ለሀገር መከላከያ ሰራዊታችን ያላቸውን አጋርነት አረጋገጡ፡፡

Want your organization to be the top-listed Government Service in Addis Ababa?
Click here to claim your Sponsored Listing.

Address

Higher Education Strategy Center 6 Kilo, International Leadership Institute Building, Second Floor
Addis Ababa