BookSiteethiopia
16/07/2025
ወደ ኢትዮጵያው እንቅስቃሴ ስንመለስ፣ በጊዜው በስታሊን ቀመር ዙሪያ መጠነኛ ውይይት ቢካሔድም ከኢትዮጵያና ኢትዮጵያዊነት ታሪክና ማንነት አንፃር ሰፊ፣ ሀገራዊና ምሁራዊ ውይይትም ሆነ ክርክር ሳላልነበረ ማነፃፀሪያ ዕውቀት አልተገኘምና ስታሊንና ሌሎች የአውሮፓ ማርክሲያውያን የጻፉትን ለመረዳት ከመታተር ባለፈ ነገሩን ወደፊት የሚገፋም ሆነ የሚጋፋ ተጨማሪ ፈር ቀዳጅ እሳቤ አልተቀመረም፡፡ በወቅቱ የብሔር ብሔረሰብ ጥያቄ ሲነሳ የተጠራጠሩና ግር ድንግርግር ያላቸው ባይጠፉም ዘልቆ ብርቱ ኀልዮታዊ ተቀናቅኖ ያቀረበ መኖሩን አላስታውስም፡፡ በእርግጥ በስሜን አሜሪካ የኢትዮጵያ ተማሪዎች ማኅበር በእነ ፕ/ር ሐጎስ ገ/እየሱስ፣ ዶ/ር እንድርያስ እሸቴ እና ዓለም ሀብቱም ጭምር በአንድ በኩል እነ ብርሃነ መስቀል መስፍን ሀብቱ በሌላ በኩል ሆነው በተከታታይ የሞቀ ክርክር አድርገውበታል፡፡ አልዘለቁበትም እንጂ፣ ትግላችን ገና በሕዝባዊ ንቅናቄ (mass movement) ደረጃ ላይ ስለሆነ ሐሳቡን ከማንሸራሸር አልፈን ልክ እንደፓርቲ ፖለቲካ ወደ ቅራኔ ውስጥ መግባትና መካረር አይገባንም በሚለው ጉዳይም ተነጋግረውበታል፡፡ በሀገር ቤትም ቢሆን የቀ.ኃ.ሥ ዩኒቨርሲቲ መምህራን በነበሩት በዶ/ር አሰፋ ምህረቱ እና መስፍን ወ/ማርያም አማካኝነት የተማሪዎች ኅብረት ባዘጋጀው የፓነል ውይይት ላይ እንዲሁ ጠንካራ ምሁራዊ መከራከሪያ ቀርቧል፡፡ ዋለልኝም ስለአቋሙ ትክክለኝነት ተከራክሯል፡፡ ሆኖም ሥራዬ ተብሎ በርእሰ ጉዳዩ ላይ በተከታታይ ስለአልተመከረበት አጠቃላይ ግንዛቤው ድፍርስ ሆኖ ከመቆየት አላመለጠም፡፡ ጉዳዩ በዋለልኝ መኮንን አማካይነትም ሆነ በቡድን ውይይታችን ወቅት በተነሳበት ጊዜ በኢትዮጵያ ውስጥ ምን ያኽል ብሔር በሔረሰቦች እንደነበሩ፣ ስማቸው፣ ቋንቋቸው፣ የሰፈሩበት አካባቢ ስፋትና ከማዕከልም የነበረው ርቀት፣ የኢኮኖሚና ማኅበራዊ ደረጃቸው፣አደረጃጀታቸውና ታሪካቸው በቅጡ አይታወቅም ነበር፡፡ ከአለፍ አገደም በ 50ዎቹ ዓመታት በዩኒቨርሲቲ የተማሪዎች ethnological Society (Bahru, 2014) አማካኝነት የተከወኑ ጭልጭልታ ጥናቶች ቢኖሩም የተወሰኑ ከመሆናቸውም በላይ ትኩረታቸው ኢትዮጵያንና ኢትዮጵያዊነትን ይበልጥ ለማወቅ ከመፈለግ አንፃር ብቻ ነበር፡፡ ከዚህ በተለየ ጉዳዩን ያነሱትም ሆኑ አዳማጩም የተለየ መረጃም ሆነ ጥልቅ ጥናት አላቀረቡልንም፡፡ እነሆ የብሔር ብሔረሰብ ነክ ሐሳቡ በነበረበት ቀጠለ፡፡ እኔም ብዥታ እንዳይፈጠር በማሰብ ማብራሪያዬንና ትንታኔዬን በጥንተ ግንዛቤውና ትርጉሙ አቅርቤዋለሁ፡፡ በዓለም አቀፍ ደረጃም ቢሆን ከ2ኛው ዓለም ጦርነት ማብቂያ በኋላ የተባበሩት መንግሥታት በጉዳዩ ላይ የራስን ዕድል በራስ ስለመወሰን ያወጣውን ድንጋጌም ሆነ የአፍሪቃ አንድነትት ድርጅት ስላለው አቋምም ጠልቆ በመግባት ያፍታታው አልነበረም፡፡ ስለሆነም የውይይቱ አልፋ ኦሜጋ በጊዜው ከነበሩ የግንጠላ ንቅናቄዎችና ከሶሺሊስት ኀልዮትና አብዮት አንፃር ብቻ ሆኖ ቆየ፡፡
በቅርቡ በመውጣት ላይ ያሉ ምሁራዊ ምርምሮችም ርእሰ ጉዳዩ በሁሉም ዘንድ እስከአሁን አካራካሪ ሆኖ እንደቀጠለ ያመለክታሉ፡ ከአስቸጋሪነቱ የተነሳም ጠቅላይ ኀልዮት እንዳልተቀረጸለት አስረግጠው ይሟገታሉ፡፡ በብሔርነትና በብሔረሰብነት መካከል ያለው ልዩነትና አንድነት፣ (በኢትዮጵያ ውስጥም ጭምር) ማን ለብሔርነት እንደሚበቃና ማንስ በብሔረስብነት ደረጃ እንዳለ ቁርቁሱ ባያባራም፣ ከዕውቀት መሻቱ ባሻገር ፖለቲካውም ስለሚዳበለው የጠራ ስምምንት አልተደረሰም፡፡ ብሔር ወይም ብሔረሰብ መሰኘትን ተከትሎ የሚመጣው የፖለቲካና ተዛማጅ የመብት ጥያቄ የተለያየ ስለሚሆን ወደ ስምምነት የመድረስ ተግዳሮቱ ቀላል አልሆነም፡፡ እንደምናውቀው የአውሮፓን ታሪክ በተመረኮዘ በተጻፈው በማርክሲያዊ አስተምህሮ መሠረት ይህን ጥያቄ ይዞ የሚነሳው የከበርቴው መደብ ነው፡፡ የዚህም ምክንያት ኋላ ቀር ከሆነው ባላባታዊ (የመሬት ከበርቴ) ወይም ፊውዳል ሥርዓት ትብታብ ራሱን በማላቀቅ ለሀብቱ የተመቸ የገበያ ሁኔታ እንዲፈጠር ስለሚፈልግ ነበር፡፡ ስለሆነም በታሪካዊ ቁስ አካልነት ፍልስፍና ስሌት መሠረት መፈክሩ እስከ ተወሰነ ደረጃ ድረስ እንደ ተራማጅ ስለሚቆጠር ኅብረተሰብ ወደፊት እንዲገፋ የሚሹ አብዮተኞች ሁሉ በመርኅ ደረጃ ይደግፉታል፡፡ በኢትዮጵያ በኩል ግን ተውተርታሪው የከበርቴ መደቡ የዚህ አቅሙም ብስለቱም ስለአልነበረው በምትኩ መፈክሩን በንዑስ ከበርቴ ተስፈኛነት የሚመደበው ተማሪ-ምሁራን ክፍተቱን በመሙላት አንስቶታል፡፡ በእርግጥም በማርክሲያዊ ኀልዮት መነጽር ስናየው በጊዜው የከበርቴ መደብ ኢትዮጵያ ውስጥ ሊፋፋበት የሚያስችለው ኢኮኖሚያዊ መሠረት ባለመዳበሩ መደቡ ይገለጽ የነበረው እንደ ብሔራዊ ከበርቴ (National Bourgeoisie) ሳይሆን እንደ ጥገኛ/አቀባባይ ከበርቴ (Comprador Bourgeoisie) ወይም ማርካኪስና ነጋ አየለ እንደጻፉት ጥምር የወታደራዊና የቡርዡዋ (military-bourgeoisie) መደብ ነበር፡፡ ይህን መሳይ መደብ ደግሞ ከጥገኝነት አልፎ ራሱን ሊጠብቅ ወይም ነፃ ሊያወጣ ስለማይችል የብሔር ነፃነት ትግልን የመምራት ብቃት እንደሌለው በኀልዮቱ ቀማሪዎች የተሰመረበት ጉዳይ ነበር፡፡
የኢትዮጵያ ተማሪዎች ትግል እና ተከታዩ የፓርቲዎች ፖለቲካ - ከጥንስሱ እስከ ድፍርሱ (1961-1970 ዓ.ም) - ግዛው ዘውዱ
27/04/2025
The Silent Patient By Alex Michaelides: The record-breaking, multimillion copy Sunday Times bestselling thriller and TikTok sensation Now Available @ BookSite Book Shop Bole Branch
Alicia Berenson lived a seemingly perfect life until one day six years ago.
When she shot her husband in the head five times.
Since then she hasn't spoken a single word.
It's time to find out why.
Visit BookSite Book Shop @ Bole Brass
ያንብቡ! የተለዩ ይሁኑ! የሚያነቡ መሪዎች ናቸው!
BookSite Bole Branch - In Front of Brass Hospital
BookSite Kazainchis Branch - Setoch Adebabaye+251 9 75 55 75 00
04/12/2024
Pay the Price
Here is a simple three-part formula for success at work: Come in a little earlier, work a little harder, and stay a little later. This will move you so far ahead of your competitors that they will never catch up.
Come into work one hour earlier, before anyone else arrives. Use that time to plan and organize your day and get started on your most important tasks. Make sure that whatever time your boss comes to work, you are always there working before he arrives.
Second, work a little harder. Don’t waste time. Don’t chat with coworkers. Work through lunchtime so that you can get on top—and stay on top—of your main tasks and responsibilities.
Third, work one hour later than your coworkers. If they leave at five o’clock, you leave at six. Use that extra time to complete your important tasks and get yourself organized for the following day.
When you come in one hour earlier, work through lunch, and work one hour later, you add three full productive hours to your day. Because there are no interruptions when you work during these time periods, you will actually accomplish two or three times as much as you would during your other work hours, when you are constantly interrupted by other people and telephone calls.
In fact, you can double or even triple your productivity, performance, and output by simply adding these three hours to your workday. The best news is that by coming in earlier and leaving later, you don’t lose anything. You merely avoid the traffic tie-ups and slow-downs that most people suffer through on their ways to and from work.
Click here to claim your Sponsored Listing.
Category
Contact the business
Telephone
Website
Address
OURSTORES: (1) BOLEINFRONTOFBRASSHOSPITAL. (2) 4KILLO,NEARBERHANINASELAMPRIN
Opening Hours
| Monday | 09:00 - 17:00 |
| Tuesday | 09:00 - 17:00 |
| Wednesday | 09:00 - 17:00 |
| Thursday | 09:00 - 17:00 |
| Friday | 09:00 - 17:00 |
| Saturday | 09:00 - 17:00 |