Joye
15/03/2026
With Sheraton Addis, a Luxury Collection Hotel – I'm on a streak! I've been a top fan for 9 months in a row. 🎉
02/06/2025
ቻይና ከኢትዮጵያም በላይ በኢትዮጵያውያን ዘንድ ተወዳጅነት አገኘች
በአዲስ አበባ ታሪካዊ የአፍሪካ አዳራሽ ይፋ በተደረገው አዲስ የአፍሪካ ምርጥ ብራንዶች ሪፖርት መሰረት፣ ቻይና በኢትዮጵያ ውስጥ እጅግ ተወዳጅ ሀገር በመሆን ኢትዮጵያን እራሷን ጭምር በልጣለች። ይህ ጥናት የውጭ ሀገራት ተፅዕኖን እና የሀገር ውስጥ ብራንዶች የሚያጋጥሟቸውን ተግዳሮቶች የሚያመላክት ነዉ ተብሏል።
በ31 ሀገራት በተካሄደው የብራንድ አፍሪካ ጥናት፣ ኢትዮጵያውያን ከሚያደንቋቸው ሀገራት ዝርዝር ውስጥ ቻይና ቀዳሚ ስትሆን፣ ኢትዮጵያ፣ ሩሲያ፣ ዩናይትድ ስቴትስ እና የተባበሩት አረብ ኤሚሬትስ ይከተሏታል።
ምንም እንኳን 68% የሚሆኑ ኢትዮጵያውያን ለአፍሪካ የወደፊት ዕጣ ፈንታ ብሩህ ተስፋ ቢኖራቸውም፣ የሀገር ውስጥ ብራንዶች ግን እውቅና ለማግኘት እየተቸገሩ ነው።
በኢትዮጵያ ከሚደነቁ 100 ምርጥ ብራንዶች ውስጥ 6% ብቻ ኢትዮጵያውያን ሲሆኑ፣ በአጠቃላይ ከሚደነቁ ብራንዶች ውስጥ 13% ብቻ የሀገር ውስጥ ናቸው። ይህ የውጭ ብራንዶች የበላይነትን እና የሀገር ውስጥ ኩባንያዎች ተጨማሪ ትኩረት እንደሚያስፈልጋቸው ያሳያል።
በአፍሪካ Nike፣ Adidas፣ Samsung፣ Coca-Cola እና Apple ከፍተኛ አምስት ተወዳጅ ብራንዶች ሲሆኑ፣ በኢትዮጵያ ደግሞ መቄዶኒያ፣ ኢትዮ ቴሌኮም እና ኮካ ኮላ "ለህብረተሰብ መልካም በመስራት" ተወዳጅነትን አግኝተዋል።
ዝርዝሩን ያንብቡ
https://capitalethiopia.com/2025/06/01/china-tops-ethiopias-admiration-rankings-surpassing-ethiopia-itself/
የኮንስትራክሽን ቴክኖሎጂ ጫፍን ማሳያ ተደርጎ የሚወሰደው የሳዑዲ አረቢያ ሰማይ ታካኪ ሕንፃ አለምን እያስደመመ ነው።
አንድ ኪሎ ሜትር የሚረዝመውና በሳዑዲ አረቢያ ግንባታው በይፋ የተጀመረው ጅዳ ታወር ሰማይ ታካኪ ሕንፃ ግንባታው ከሦስት አመት በኃላ በ2028 ዓ.ም ሊጠናቀቅ ይችላል።
በግንባታው ዘመን አመጣሽ አዲስ ቴክኖሎጂ ለመጀመሪያ በተግባር ላይ ውሏል። የሕንፃው ግንባታ የመጀመርያ ምዕራፍ እየተካሄደ ያለው በ4D ሞዴል ቴክኖሎጂ ሲሆን፣ ይህም ሞዴል በFreeform 3D የተፈጠረ ከመሆኑም በላይ፣ ቴክኖሎጂው ሰማይ ጠቀሱ ህንፃ እንዴት እንደሚጠናቀቅ ከማሳወቁም በላይ አመላካች የማጠናቀቂያ ቀናትንም በውስጡ አካቶ ይዟል።
ግንባታው ሙሉ በሙሉ ከተጠናቀቀ የዱባይ 828 ሜትር ቡርጅ ካሊፋን የሚበልጥ አዲሱ የዓለማችን ረጅሙ ህንፃ ይሆናል።
📷 Freeform 3D / SBG
14 ባንኮች በተሳተፉበት ስድስተኛው የውጭ ምንዛሪ ጨረታ የአንድ የአሜሪካ ዶላር አማካይ ዋጋ 133 ብር ሆኖ ተመዘገበ
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ 50 ሚሊዮን ዶላር ያቀረበበት በዚህ ስድስተኛው ዙር የውጭ ምንዛሪ ጨረታ፣ 14 ባንኮች ተሳትፈውበታል። የአንድ ዶላር አማካይ ዋጋ 133.17 ብር ሆኖ ሲመዘገብ፣ ከ16 ቀናት በፊት በተካሄደው አምስተኛው ዙር ጨረታ የአንድ ዶላር ዋጋ 132.9 ብር እንደነበር ይታወቃል። ይህም መጠነኛ የዋጋ ጭማሪ አሳይቷል።
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የውጭ ምንዛሪ ገበያን ለማረጋጋትና የውጭ ምንዛሪ መረጋጋትን ለመቆጣጠር ያለመ ይህን ጨረታ በየሁለት ሳምንቱ እንደሚያካሂድ ማሳወቁ ይታወሳል።
ባለፈዉ በተደረገዉ አምስተኛ ዙር ጨረታ ባንኩ 60 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር ያቀረበ ሲሆን፣ በጠቅላላው 16 የንግድ ባንኮች የውጭ ምንዛሪ ድልድል ማግኘት ችለው ነበር። የዘንድሮው ጨረታ ግን የቀረበውን የዶላር መጠን ወደ 50 ሚሊዮን ዝቅ አድርጎታል።
Parent-teacher-associations can play an important role to make sure children are enrolled in school, learning and well-supported - this is especially meaningful for girls and children with disabilities.
Together, GPE and UNICEF South Sudan helped to train members of parent-teacher-associations in 🇸🇸 , improving their capacities to focus on school development, resource mobilization, goal setting and financial management.
Members of the association are happy with the results of the training:
👉 Now, they are able to better engage with community members and bring out-of-school children back to the classroom while using their resource mobilization skills to fund school activities, support volunteer teachers and carry out minor repairs in classrooms.
Click here to claim your Sponsored Listing.
Category
Contact the public figure
Telephone
Website
Address
Addis Ababa
Opening Hours
| 12:00 - 06:00 |