Awash Bank S.C
09/05/2020
ሚያዝያ 30/2012 ዓ.ም
አዲስ አበባ
በጎ ፍቃደኞች አሁንም ስራ ላይ ናቸው
===============================
የአዲስ አበባ ትራፊክ ማኔጅመንት ኤጀንሲ ስራዎችን እያገዙ ከሚገኙ አካላት የበጋ ወቅት በጎ ፍቃደኛ የትራፊክ አስተናባሪዎች ግንባር ቀደም ተጠቃሽ ናቸው፡፡
ከ550 በላይ የበጋ ወቅት በጎ ፍቃዳኛ ወጣቶች እና እናቶች በከተማዋ ዋና ዋና መንገድ አደባባዮች እና የባቡር መሻገሪያዎች ላይ የትራፊክ ፍሰቱን የማስተናበር እንዲሁም በተለያዩ የተግባቦት አግባቦች የመንገድ አጠቃቀም እና መወሰድ ስላለባቸው ጥንቃቄዎች ግንዛቤ እየሰጡ ይገኛሉ፡፡
በጎ ፍቃደኞቹ የወቅቱ ወረርሽኝ ኮሮና (ኮቪድ 19) ቫይረስ በሽታ ሳይበግራቸው ተገቢውን ጥንቃቄ እያደረጉ የማስተነባሩን ስራ ቀጥለውበታል፡፡ በወጣቶቹ የማስተናበር ስራ በተለይ ህዝብ በሚበዛባቸው አደባባዮች እና የባቡር መሻገሪያዎች አካባቢ እግረኞች ተገቢውን ጥንቃቄ በማድረግ ያለስጋት እንዲንቀሳቀሱ አሽከርካሪዎችም ለእግረኛው ቅድሚያ በመስጠት እንዲያሽከረክሩ በማድረግ በተሰማሩበት አካባቢዎች የትራፊክ አደጋ እንዲቀንስ እያደረጉ ይገኛሉ፡፡
ኤጀንሲው ለወጣቹ አስፈለጊዉን ክትትልና ድጋፍ እያደረገላቸው ያለ ሲሆን የኤጀንሲው ደቡብ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት የመንገድ ደህንነት እና አቅም ግንባታ ቡድንም በአቃቂ ቃሊቲ እና ንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከቶሞች በስራ ላይ ለሚገኙ ወጣቶች ተከታታይ ድጋፍና ክትትል በማድረግ እራሳቸውንም ከኮሮና ቫይረስ እንዲጠብቁ እያደረግኩ ነው ብሏል፡፡
የህዝብ ግንኙነትና ኮሙዩኒኬሽን ቡድን
011 667 34 55
ሰላማዊና ተቀባይነት ያለው የትራፊክ እንቅስቃሴን ለማረጋገጥ እንሰራለን!
Click here to claim your Sponsored Listing.