Grand Ethiopian Renaissance Dam,Addis Ababa
26/02/2026
ዜና ሹመት
የካቲት 19/2018ዓ.ም
ወ/ሮ መቅደስ አዱኛ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ህዝባዊ ተሳትፎ ማስተባበሪያ ፕሮጀክት ጽ/ቤት ምክትል ስራ አስኪያጅ ሆነው ተሾሙ።
በእለቱም ከቀድሞዋ ም/ስራ አስኪያጅ ወ/ሪት አንቺነሽ ተስፋዬ ጋር የስራ ርክክብ አድርገዋል ። ወ/ሮ መቅደስን በጸ/ቤታችን ስም እንኳን ደህና መጡ ለማለት እንወዳለን።
26/02/2026
የፕሮጀክት ጽ/ቤቱ አመራርና ባለሙያዎች ከክ/ከተማ የህዳሴ ጽ/ቤት ኃላፊዎች ጋር በመሆን የቀድሞ የጽ/ቤቱን ምክትል ስራ አስኪያጅ የሽኝት መርሃ ግብር አዘጋጁ።
የሽኝት መርሃግብሩን በንግግር የከፈቱት የጽ/ቤቱ ዋና ስራ አስኪያጅ ወ/ሮ ንዒመተላህ ከበደ የቀድሞ የጽ/ቤታችን ም/ስራ አስኪያጅ የነበሩትና አሁን የቦሌ ክፍለ ከተማ ምክትል ስራአስፈፃሚና የስራና ክህሎት ጽ/ቤት ኃላፊ የሆኑት ወ/ሪት አንቺነሽ ተስፋዬ በስራ ሂደት ስለነበራቸው የአብሮነት ቆይታ አመስግነው አሁን የተሰጣቸውን ኃላፊነትም በብቃት እንደሚወጡና ብቃት ያላቸው አመራር እንደሆኑ ገልፀዋል። ከክ/ከተማና ከማዕከል የባለሙያ ተወካዮችም በስራ በቆዩበት ወቅት ስለነበራቸው መልካም ግንኙነት አመስግነው መልካም የስራ ዘመን እንዲገጥማቸው ምኞታቸውን በመግለፅ የሽኝትና የምስጋና መርሃ ግብሩ ተጠናቋል።
06/02/2026
የከተማችንን ጐስቋላ ገፅታ በመቀየር ውብ፣ ፅዱ እና አረንጓዴ ለነዋሪዎቿ ምቹ፣ ለጐብኝዎች ሳቢና አለማቀፍ ተወዳዳሪ እንድትሆን በ24/7 የስራ መርሀ ግብር ሰርተን ውጤት ያስመዘገብንበት ነው ።
ከንቲባ አዳነች አቤቤ
05/02/2026
“በአፍሪካ ዝቅተኛ የኤሌክትሪክ ኃይል እንዲሁም የውሃ ታሪፍ በማቅረብ ረገድ ኢትዮጵያ በየጊዜው በአንደኝነት ትጠቀሳለች!” - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)
Click here to claim your Sponsored Listing.
Category
Contact the organization
Telephone
Website
Address
Addis Ababa
1000