ASCHO Mng
26/05/2024
#ስኳር ያለባቸው ነፍሰ ጡር እናቶች ኢንሱሊንን ሆድ ላይ መወጋት ይችላሉን?
አብዛኛዎቹ ነፍሰ ጡር እናቶች ኢንሱሊን ሆድ ላይ ለመወጋት ይፈራሉ፣ መርፌው ጽንሱን ይጎዳዋል ብለው ይጨነቃሉ። የስኳር ህመም ላለባቸው ነፍሰ ጡር እናቶች ኢንሱሊን ለመውጋት ተመራጩ ቦታ ሆድ ነው። በእርግዝና ወቅት ኢንሱሊንን ሆድ ላይ መውጋት ደህንነቱ የተጠበቀ ነው። ሆድ ኢንሱሊንን ለመውሰድ ቀላልና አመቺ ቦታ ብቻ ሳይሆን ኢንሱሊን ወደ ሰውነት በአስተማማኝ ሁኔታ እንዲገባ (predictable insulin absorption rate) ስለሚረዳ ለኢንሱሊን አወሳሰድ የሚመከር ቦታ ነው። የኢንሱሊን መርፌው ለጽንሱ ምንም አይነት ስጋት አይፈጥርም ምክንያቱም ማህፀኑ ጽንሱን በበቂ ሁኔታ ከለላ ይሰጠዋል። ስለዚህ, የመጀመሪያ ጥያቄያችንን ለመመለስ, አዎ, በእርግዝና ወቅት ኢንሱሊን ሆድ ላይ መውጋት በአጠቃላይ ደህንነቱ የተጠበቀ ነው።
በእርግዝና ወቅት ኢንሱሊንን ሆድ ላይ መውጋት ደህንነት ካረጋገጥን በመቀጠል በተለያዩ የእርግዝና ወቅቶች መደረግ ስላለባቸው የተወሰኑ ምክሮችን ስናይ
1. በመጀመሪያው ሶስት ወር የእርግዝና ጊዜ (first trimester) የኢንሱሊን መርፌ በየትኛውም የሰውነት ክፍል ላይ መወጋት ይቻላል:: ከእርግዝና በፊት የነበረ ስኳር ያለባቸውና ኢንሱሊን የሚወስዱ እናቶች የመጀመሪያው ሶስት ወር የኢንሱሊን መውጊያ ቦታ ወይም ቴክኒክ ለውጥ አያስፈልግም።
2. በሁለተኛው ሶስት ወር (second trimester) ጊዜ ሲደርስ የሆድ ገጽታ መለወጥ ይጀምራል፤ ጽንሱ ያድጋል እና ሆድም እንዲሁ። ይሁን እንጂ ኢንሱሊን ሆድ ላይ መውጋት መተው አለብን ማለት አይደለም። ይልቁንስ የመርፌ መወጊያ ቦታን መጠነኛ ማስተካከያ ማድረግ ይችላሉ።በእምብርት ዙሪያ ከጽንሱ ፊት ለፊት ያለውን የሆድ ክፍል ይልቅ ጽንሱ ካለበት በደንብ ራቅ ብለን ከጎን ያሉት የሆድ ክፍሎች ኢንሱሊንን ለመወጋት መጠቀም ይቻላል።
3. በመጨረሻ ሶስተኛው ወር (third trimester) ልጁ እያደገ የመርፌ መወጊያ ቦታ እየጠበበ ይሄዳል እንዲሁም ቆዳ በሆድ ላይ በጣም ጥብቅ ሊል ይችላል። እንዳንዴ ለኢንሱሊን መርፌ መወጊያ የሚሆን ምቹ ቦታ ማግኘት ሊከብድ ይችላል። እንዲህ ሲያጋጥም አይጨነቁ ፣ መፍትሄ አለ ።
መምረጥ ያለብን ቦታ በጎን የሆድ ክፍል ያለውን መሆን አለበት። ቦታውን በአውራ ጣት እና ጠቋሚ ጣት መሀል ቆንጠጥ በማድረግ ቆዳውን ትንሽ በማንሳት መወጋት ይቻላል:: ከሆድ ጋር ጥብቅ ያለውን ሳይሆን በጣቶች መሃከል ላይ ቆዳን ከፍ ማድረግ የሚቻልበት ቦታ በሆድ ጎን ላይ ያግኙ። ከዚያም መርፌውን ከቆዳ በ90 ዲግሪ ቀጥታ አስገብቶ መውጋት ይቻላል።
ይህ ዘዴ ምቹ እና ውጤታማ ሲሆን የኢንሱሊን መርፌን ለመወጋት ተመራጭ መንገድ ነው። ከተገኘ በጣም አጭር የኢንሱሊን መርፌ (በ4 ሚሊ ሜትር) መጠቀም ጥሩ ነው። ይህን የማይመርጡ እና ጽንሱን እንዳልውጋው የሚል ከፍተኛ ፍርሃት ያለባቸው እናቶች እንደአማራጭ ክንድ፣ ታፋ ወይም መቀመጫ ላይ ሊወጉ ይችላሉ።
03/02/2024
የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ መልዕክት ‼️
የወቅቱ የመስኖ ስንዴ ምርታማነት በጥቂቱ። የግብርና አቅማችንን በምሉዕ እንጠቀም ዘንድ የጋራ ጥረታችን የጀመርነውን የስራ ፍጥነት ጠብቆ እንዲሄድ እንረባረብ።
28/01/2024
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በተባበሩት መንግሥታት የምግብ እና የእርሻ ድርጅት፣ በሮም ጣልያን በተሰናዳ ክብረ በዓል የከበረውን የፋኦ አግሪኮላ ሜዳልያ ተሸልመዋል።
ሽልማቱ ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር በምግብ ዋስትና እና በተመጣጠነ የምግብ አቅርቦት ላሳዩት ርዕይ፣ አመራር እና ቁርጠኝነት፣ ብሎም ፈጣን፣ ተለዋዋጭ እና ፈታኝ በሆነው ከባቢያዊ ሁኔታ በስንዴ ምርት ራስን ለመቻል በተከተሉት ፈጠራዊ መፍትሔ ዕውቅና ለመስጠት የተበረከተ ነው።
ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር የተለያዩ ሀገራት ከፍተኛ ልዑካን ቡድኖች፣ የዓለም አቀፍ ተቋማት ተወካዮች፣ በጣልያን የሚገኙ የዲፕሎማቲክ ተልዕኮዎች አባላት እንዲሁም የግሉ ዘርፍ ተወካዮች በተገኙበት ሽልማቱን ተቀብለዋል።
ኢትዮጵያ ላለፉት አምስት ዓመታት በግብርናው መስክ ቁልፍ ኢንቨስትመንቶችን ያደረገች ሲሆን በስንዴ ምርት ራስን የመቻል ሥራዎችን በማከናወን በዐበይት ምርቶችም ላይ ከፍተኛ ዕድገት አስመዝግባለች።
In a ceremony hosted by the United Nations Food and Agriculture Organization in Rome, Italy, Prime Minister Abiy Ahmed has been awarded the prestigious FAO Agricola Medal, according to the organization, for his vision, leadership and commitment to food security and nutrition as well as the pursuit of innovative solutions in wheat self-sufficiency in the context of fast-changing and challenging circumstances.
The Prime Minister received the Agricola Medal in the presence of high-level delegates of various countries, representatives of international organizations, diplomatic missions in Italy and private sector representatives.
For the past five years, Ethiopia has been making critical investments in the agricultural sector and pursuing wheat self sufficiency endeavors marking significant growth across major commodities.
Click here to claim your Sponsored Listing.