Ghion Stream
28/07/2022
ጣና ዳር
ውቢቷ ባህር ዳር
28/07/2022
በአማራ ክልል ርእሰ መሥተዳደር ይልቃል ከፋለ (ዶ.ር) አቅራቢነት የአማራ ክልል ምክር ቤት የተለያዩ ሹመቶችን አጸደቀ።
ርዕሰ መስተዳድሩ ለክልሉ ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ ኃላፊነት፣ ለዋና ኦዲተር መሥሪያ ቤት ምክትል ዋና ኦዲተር እና ለንጋት ኮርፖሬት የቦርድ አባላት እጩ ተሿሚዎችን ለምክር ቤቱ አቅርበዋል። ምክር ቤቱም የቀረቡ እጩ ተሿሚዎችን ተቀብሎ ሹመታቸውን አጽድቋል።
በዚህ መሠረት:-
1.አቶ እርዚቅ ኢሳ - የአማራ ክልል የወጣቶች እና ስፖርት ጉዳይ ቢሮ ኃላፊ
2. አቶ ሰውበሰው ብዙዓየሁ- የአብክመ ዋና ኦዲተር መሥሪያ ቤት ምክትል ዋና ኦዲተር ሆነው ተሹመዋል።
ምክር ቤቱ የንጋት ኮርፖሬት የቦርድ አባላትን ሹመትም አጽድቋል።
1.አቶ ስዩም መኮንን -የንጋት ኮርፖሬት የቦርድ ሰብሳቢ
2.ወይዘሮ ዓይናለም ንጉሤ-የንጋት ኮርፖሬት ምክትል ቦርድ ሰብሳቢ
3.ዶክተር ስንታየሁ ወልደ ሚካኤል-አባል
4.ዶክተር አሕመዲን አሕመድ-አባል
5.ዶክተር ጥላሁን መሐሪ -አባል
6.ዶክተር አሥራት አጸደወይን-አባል
7.አቶ አርማዬ ገላው -አባል
8.ወይዘሮ ባንች አምላክ ገብረ ማሪያም-አባል
9.ዶክተር ጋርዳቸው ወርቁ-አባል ኾነው ተሹመዋል።
Click here to claim your Sponsored Listing.