I Hope
09/02/2026
ኢትዮጵያን ወግቶ አሸናፊ መሆን አይቻልም"
የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ክቡር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
09/02/2026
ኢትዮጵያ ለሰላም ያላትን ቁርጠኝነት ስታሳይ ፣ ኤርትራ ግን ቀጠናውን የማተራመስ ፍላጎቷን በግልጽ አሳይታለች !!
ገንቢ የሆነ የዲፕሎማሲ ግንኙነት በጥርጣሬና የተሸሸጉ ፍላጎቶችን በመፈለግ ላይ ሳይሆን ፣ ትኩረትን ዋና ዋና የቀጠናው ጉዳዮች ላይ በማድረግ ችግሮችን መፍታትን ይጠይቃል።
ኢትዮጵያ ይህንን መርህ መሠረት በማድረግና ለቀጠናው ሰላም ቅድሚያ በመስጠት ፣ ልዩነቶችን በጠረጴዛ ዙሪያ ለመጨረስ ያላትን ቁርጠኝነት በግልጽ ደብዳቤ ብታሳውቅም ፣ በኤርትራ በኩል ግን ለቀረበው የሰላምና የውይይት ጥሪ ተገቢውን ምላሽ ከመስጠት ይልቅ ጉዳዩን ወደ ጎን በመተው ለውይይት ዝግጁ አለመሆኗን በግልጽ አሳይታለች።
ኢትዮጵያ አሁንም ቢሆን በሰላማዊ መንገድ ለመሳተፍ ያላትን ዝግጁነት እየገለጸች ባለችበት በዚህ ወቅት ፣ የኤርትራ እምቢተኝነት በቀጠናው የተረጋጋ ግንኙነት ለመፍጠር የሚደረገውን ጥረት የሚያደናቅፍና ሃገሪቱ ለሰላማዊ አማራጮች ያላትን ዝቅተኛ ፍላጎት የሚያንጸባርቅ ከመሆኑም በላይ የሻዕቢያ መንግስት ለቀጠናው አለመረጋጋት ዋና ተጠያቂ የሚያደርግ ነው።
Click here to claim your Sponsored Listing.
Category
Culinary Team
Attire
Telephone
Website
Address
Addis Ababa