Addis Guday

Addis Guday

Share

Photos from Addis Guday's post 23/04/2026
Photos from Addis Guday's post 21/04/2026

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ተጠያቂነትንና የአሰራር ግልፅነትን ለማጎልበት የተዘጋጀውን ደንብ አጸደቀ

- ሌሎች ውሳኔዎችንም አሳልፏል፣

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ካቢኔ ዛሬ ባካሄደው 5ኛ ዓመት 10ኛ መደበኛ ስብሰባ በሶስት ረቂቅ ደንቦች ላይ ተወያይቶ ተፈጻሚ እንዲሆኑ አጽድቋል።

በስብሰባው በቀረቡ አጀንዳዎች ላይ ከተወያየ በኋላ ሶስት ረቂቅ ደንቦች ተፈጻሚ እንዲሆኑ ውሳኔ አስተላልፏል።

በዚህም መሰረት:-

💢 የተሻሻለ የፋይናንስ አስተዳደርን ይበልጥ ለማዘመን፣ ተጠያቂነትንና የአሰራር ግልፀኝነትን ለማጎልበት የተዘጋጀው ረቂቅ ደንብ ተፈጻሚ እንዲሆን፣

💢 በከተማዉ እየተገነባ ያለው ሰፊ የቤት ልማት የተሻለ አፈፃፀም እንዲኖረው፣ የቤቶች ኮርፖሬሽን ሪፎርምን ለማጠናከር እና የማስፈፀም ብቃት ለማሳደግ የተዘጋጀዉን ረቂቅ ደንብም አፅድቋል።

💢 የመሬት ማስፋፊያ ለጠየቁ ተኪ ምርት ለሚያመርቱ ኢዱስትሪዎች፣ ለወጣቱ የስራ ዕድል የፈጠሩ ፕሮጀክቶች፣ ሆቴሎች እንዲሁም፥ በከተማ አስተዳደሩ ከሐይማኖት ተቋማት ጋር በተደረጉ ተከታታይ ውይይቶች የተነሱ የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎችን መፍታት የሚያስችል መሬት በምደባ ለማስተላለፍ የቀረበው የውሳኔ ሀሳብ ተፈፃሚ እንዲሆን በስብሰባው ወስኗል።
ምንጭ ከ #ድሬቲዩብ

Want your business to be the top-listed Beauty Salon in Addis Ababa?
Click here to claim your Sponsored Listing.

Website

Address

Addis Ababa
1621