Great silte

Great silte

Share

Photos from Mehdi Ahmed Abdela's post 17/12/2023
Photos from Great silte's post 02/09/2023

ግልጽና አጭር መልዕክት ለፌደራሉ መጅሊስ አዲስ አበባ


ለሴት ተማሪዎች ኒቃብ ለብሶ ትምህርት መማር ክልክል ነው የሚል ግልጽ ሃገር አቀፍ አዋጅ በሌለበትና በሌሎች አካባቢዎች ላይ ኒቃብ አድርገው እየተማሩ የሚገኙ ተማሪዎች ባለበት ተጨባጭ ላይ…የጉራጌ ዞን ጉንችሬ ከተማ ሙስሊም ጠሎች ግን የግል ጥላቻቸውን ተቋማዊ በማድረግ የበርካታ ሙስሊም የእህቶቻችንን ህገ መንግስታዊና ሰብዓዊ መብት በማን አለብኝነት ስሜት እየጣሱ ይገኛሉ !!

ይህም አሳዛኝ ግፍና ጥቃት ከአካባቢው የሙስሊም ተወካዮችና ማህበረሰብ አቅም በላይ መሆኑም ተደጋግሞ ታይቷል !!

በመሆኑን ይህን መሰሉ የጉንችሬ ከተማ የሙስሊም ጠሎች አስነዋሪ ተግባርና ድርጊት በመላው ሙስሊም ማህበረሰብ ላይ የተቃጣና የተፈጸመ በደል መሆኑን የፌደራል መጅሊሡ ግንዛቤ ወስዶ እንደ አንድ ግዙፍ ማህበረሰብ ተወካይነቱ በሙስሊም ሴት ተማሪዎች ላይ እየተፈጸመ ያለውን በደልና ግፍ ለሚመለከታቸው ተቋማት በማሳወቅና ብርቱ ክትትል በማድረግ ከዚህ በተጨማሪም በተቋሙ የህግ ክፍል አስቸኳይ የህግ ተጠየቅ እንቅስቃሴን በማስጀመር ህጋዊ መብትን የማስከበር እርምጃ ይወሰድ ዘንድና በየግዜው የተሄደበትን አቅጣጫና የተገኘውን ምላሽ በይፋዊ መግለጫ ያሳውቅ ዘንድ አጥብቀን እንጠይቃለን !!
___________________________

17/08/2023

አልሀምዱሊላህ!
በጠሮ መስጂድ ጉዳይ ታስረው የነበሩ አባቶች መፈታታቸው ተገለፀ።

ሃሩን ሚድያ ነሀሴ10/2015

በጠሮ መስጂድ በተከሰተው ችግር ምክንያት በሀሰት ታስረው
በሸዋ ሮቢት ማረሚያ ቤት ይገኙ የነበሩ ሁሉም አባቶች ከእስር ተፈተው አ.አ ገብተው ከቤተሰብ ጋር ተቀላቅለዋል።

ሃሩን ሚድያ በቅርቡ የጠሮ መስጂድ ጉዳይን አስመልክቶ የሚመለከታቸውን የአካባቢው ነዋሪዋች አናግሮ ዘገባ መስራቱ ይታወሳል የአዲስ አበባ መጅሊስም የጠሮ መስጂድ የተፈጠረውን ያለመግባባት በቅርቡ እንደሚፈታ የአዲስ አበባ መጅሊስ ዋና ፀሀፊ የሆኑት ሼህ ሁሴን በሽር ለሀሩን ሚድያ ገልፀዋል።

©ሃሩን ሚድያ

Want your business to be the top-listed Food & Beverage Service in Addis Ababa?
Click here to claim your Sponsored Listing.

Website

Address

Addis Ababa