Osho
07/11/2022
...ከራስህ ተሞክሮ በመነሣትም ታውቀዋለህ። በስቃይ፣ በእንግልት ውስጥ ስትሆን እግዚአብሔርን ታስታውሳለህ። ደስተኛ ስትሆን፣ ሕይወትም ፈንጠዝያ ስትሆን ስለፈጣሪ ምንም አትጨነቅም፤ አታስታውስምም። ቀላል ተሞክሮ ነው፤ ለማየት ሳይኮሎጂስት አያስፈልግም። ሁሉም በራሱ ሕይወት ሊያስተውለው ይችላል።
በርግጥ ነገሮች ጥሩ ስሄዱ ወደ ቄስ ሄደህ አታውቅም ነበር። ነገሮች ውብ ሆነው ስሄዱ፣በሕይወትም ስኬታማ ስትሆን፣ ሕይወትም የአበባ ማስቀመጫ ስትሆን፣ ፈጣሪን አላስታወስክም። ሕይወት የብስጭት ቦታ ስትሆን ግን በድንገት እግዚአብሔርን ታስታውሳለህ።
#እግዚአብሔር ማምለጫህ ይሆናል።
👇
31/10/2022
የህይወት ጣእሙ የጠፋባቸው ሰዎች አሉ፤ በየእለቱ ተመሳሳይ ሕይወት የሚኖሩና በሕይወታቸው ውስጥ አዲስ ክስተት አጥተው ስልቹ የሆኑ ሰዎች አሉ። |
ሕይወትን በማሰብ ( በአእምሮ ) ብቻ የሚኖሯት ሰዎች ሕይወት ትርጉም አልባ ሆናባቸዋለች። ኦሾ የምዕራባውያንን ፈላስፎች የሚከሳቸው አንደኛው በዚህ ነው ፣ "ሕይወትን በአእምሮ ተግባራት ብቻ በመሙላት አሰልቺ ያደረጉ ፤ የልብ ቋንቋ የማይገባቸው ፤" ይላቸዋል።
ህይወትን በአእምሮ ሳይሆን በልብ ኑሯት ፤ ህይወታችሁን በልባችሁ ቋንቋ ስትመሯት አእምሯችሁ ታላቅ ተፈጥሮውን ያሳያችኋል፡፡ በአእምሯችሁ ስትኖሩ ፖለቲከኛ ፣ ዘረኛ ፣ አክራሪ ... ወዘተ ትሆናላችሁ ፤ በልባችሁ ስትኖሩ ግን መንፈሳዊ ትሆናላችሁ። በልባችሁ ስትኖሩ የህይወት ጣዕሙ ይገባችኋል፤ የፍቅር ሙቀቱ ይሰማችኋል፡፡
ተልእኳችሁን ስታቁና በተሰጥኦዋችሁ ስትኖሩ የሕይወታችሁ ገዢ ሀይል ከልባችሁ ይመነጫል፤ አእምሯችሁም የልባችሁ ታዛዥ ይሆናል፡፡ ሴቶች ከወንዶች የሚበልጡትና ከወንዶች ይልቅ ደስተኞች የሆኑት ለዚህ ነው፤ ወንድ ሕይወቱን የሚዘውረው በአእምሮው ሲሆን ፣ የሴቷን ሕይወት የሚዘውረው ግን ልቧ ነው፡፡
ከአእምሮ ሎጂክና ምክንያት ሲወጣ ፣ ከልብ ግን ፍቅር ይወጣል። ሎጂክና ምክንያት ብዙ ነገሮችን ትርጉም አልባ እና አሰልቺ ሲያደርጋቸው፤ ፍቅር ግን እያንዳንዱን የሕይወት ስንጣሪ በትርጉም የተሞላችና አስደሳች ያደርጋታል።
Please and
https://t.me/EthioOsho
Click here to claim your Sponsored Listing.